አየር ሃይሉ 167 የሩሲያ ሰው አልባ አውሮፕላኖችን ለመምታት በካሄደው ዘመቻ ነው 106 ድሮኖችን መትቶ መጣል የቻለው፡፡
ሰው አልባ አውሮፕላኖቹ በዩክሬን ኦዴሳ፣ ኪየቭ፣ ሱሚ እና ቼርካሲ ግዛቶች ላይ ጥቃት ለመፈጸም ሲንቀሳቀሱ ርምጃ እንደተወሰደባቸው መገለጹን ቢቢሲ ዘግቧል፡፡
የዩክሬን ፕሬዚዳንት ቮሎድሚር ዘለንስኪ÷ሩሲያ የወደብ ከተማ በሆነችው ኦዴሳ በፈጸመችው ተዳጋጋሚ ጥቃት ከ160 ሺህ በላይ ዩክሬናዊያን የሃይል አገልግሎት ማግኘት እንዳልቻሉ ተናግረዋል፡፡
አየር ሃይሉ በሰው አልባ አውሮፕላኖች ላይ የወሰደው የመከላከል ርምጃም ሩሲያ በዩክሬን ከተሞች ላይ የምትፈጽመውን ጥቃት እንደሚቀንስ አመላክተዋል፡፡
ፋና
More Stories
ዜጎች በመልዕክት መላላኪያ አማራጮች በሚፈጸሙ የሳይበር ጥቃቶች ተጋላጭ እንዳይሆኑ ጥንቃቄ ማድረግ ይኖርባቸዋል፡-የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር
በሸካ ዞን አስተማማኝና ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥ እና የህግ የበላይነትን ለማስከበር ያለመ ዞናዊ የፀጥታ ግብረ ኃይል የምክክር መድረክ በቴፒ ከተማ ተካሄደ
ክልላዊ የተቀናጀ የማኅበረሰብ አቀፍ ተፋሰስ ልማት ማብሰሪያ ፕሮግራም በመካሄድ ላይ ይገኛል።