የማሻ ወረዳ ምክር ቤት ዋና አፌ ጉባኤ አቶ አድሳለም ገብሬ በመድረኩ እንደገለጹት ምክር ቤቶች ህገ-መንግስቱ በተሰጠው ስልጣን መሠረት ሕግ-አውጭ ፤ሕግ-አስፈፃሚ እና ሕግ-ተርጓሚው ያከናወኗቸውን ተግባራት ለሕዝብ ቀርቦ የሚገመግምበት መሆኑን ተናግረዋል ።
ጉባኤውም የማሻ ወረዳ ምክር ቤት ያለፈውን መደበኛ ጉባኤ ቃሌ ጉባኤ መርምሮ ማፅደቅ፣ የቀረበ ሹመት ማፅደቅን ጨምሮ በተለያዩ አጀንዳዎች ዙሪያ ከምክር ቤት አባላትና ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር ውይይቶችና ምክክሮች ተደርጎ ቀጣይ አቅጣጫዎች ይቀመጣሉ ተብሎ ይጠበቃል ።
በወረዳው ባለፉት ግማሽ በጀት ዓመትም የተከናውኑ አፈፃፀም ሪፖርት በሚመለከታቸው ባለድሪሻ አካላት ቀርቦ ውይይት ይደረጋል ።
ጉባኤውም ለተከታታይ ሁለት ቀናት በተለያዩ አጀንዳዎች ላይ ይመክራል ተብሎ ይጠበቃል ።
More Stories
በህዝቦች መካከል ያለዉን ትስስር ይበልጥ ለማጠናከርና ዘላቂ ሰላምና ልማት እንዲረጋገጥ የየአካባቢዉን ባህላዊ የግጭት አፈታት ዜዴ በዘላቂነት ማስቀጠል እንደሚገባ ጥሪ ቀረበ።
የ2018 በጀት ዓመት የካፒታል ፕሮጀክቶች የበጀት ዕቅድ እየተገመገመ ነዉ።
አቶ ጌታቸው ረዳ እና የመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስትር አብርሃም በላይ በአዲስ አበባ ከሚኖሩ የትግራይ ተወላጆች ጋር በትግራይ ክልል ወቅታዊ ሁኔታ ዙሪያ ውይይት እያደረጉ ነው።