የዩክሬኑ ፕሬዚዳንት ቮሎድሚር ዘለንስኪ አገራቸው ጦርነቱን በሰላም ለመቋጨት በተካሄደው የሳውዲ አረቢያ የሰላም ንግግር ላይ እንድትገኝ አለመጋበዟ የሚያስገርም ነው ማለታቸውን ተከትሎ ትራምፕ ጠንከር ያለ ወቀሳ አቅርበዋል።
የዩክሬን ምላሽ ያልጠበቁት እንደሆነ የገለፁት ትራምፕ፤ ለጦርነቱ ጅማሮ ዩክሬንን ተጠያቂ አድርገው አገሪቱ “ስምምነት ላይ መድረስ ትችል ነበር” ብለዋል።
ባለፉት ሶስት ዓመታት ይህን ማድረግ ይችሉ ነበር፤ ችግሩ በቀላሉ ሊፈታ ይችል ነበር ሲሉ ትራምፕ ተናግረዋል።
እንደ ቢቢሲ ዘገባ፥ ዩክሬን ጦርነቱን መጀመር አልነበረባትም፤ ስምምነት ላይ መድረስ ትችል ነበር ብለዋል።
ይህም ከሞላ ጎደል ሁሉንም መሬት ያስገኝላት ነበር፤ ሰዎች አይሞቱም ነበር፣ ከተሞችም አይፈርሱም ነበር ሲሉ ነው ትራምፕ የተናገሩት።
More Stories
ዜጎች በመልዕክት መላላኪያ አማራጮች በሚፈጸሙ የሳይበር ጥቃቶች ተጋላጭ እንዳይሆኑ ጥንቃቄ ማድረግ ይኖርባቸዋል፡-የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር
በሸካ ዞን አስተማማኝና ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥ እና የህግ የበላይነትን ለማስከበር ያለመ ዞናዊ የፀጥታ ግብረ ኃይል የምክክር መድረክ በቴፒ ከተማ ተካሄደ
ክልላዊ የተቀናጀ የማኅበረሰብ አቀፍ ተፋሰስ ልማት ማብሰሪያ ፕሮግራም በመካሄድ ላይ ይገኛል።