የዩክሬኑ ፕሬዚዳንት ቮሎድሚር ዘለንስኪ አገራቸው ጦርነቱን በሰላም ለመቋጨት በተካሄደው የሳውዲ አረቢያ የሰላም ንግግር ላይ እንድትገኝ አለመጋበዟ የሚያስገርም ነው ማለታቸውን ተከትሎ ትራምፕ ጠንከር ያለ ወቀሳ አቅርበዋል።
የዩክሬን ምላሽ ያልጠበቁት እንደሆነ የገለፁት ትራምፕ፤ ለጦርነቱ ጅማሮ ዩክሬንን ተጠያቂ አድርገው አገሪቱ “ስምምነት ላይ መድረስ ትችል ነበር” ብለዋል።
ባለፉት ሶስት ዓመታት ይህን ማድረግ ይችሉ ነበር፤ ችግሩ በቀላሉ ሊፈታ ይችል ነበር ሲሉ ትራምፕ ተናግረዋል።
እንደ ቢቢሲ ዘገባ፥ ዩክሬን ጦርነቱን መጀመር አልነበረባትም፤ ስምምነት ላይ መድረስ ትችል ነበር ብለዋል።
ይህም ከሞላ ጎደል ሁሉንም መሬት ያስገኝላት ነበር፤ ሰዎች አይሞቱም ነበር፣ ከተሞችም አይፈርሱም ነበር ሲሉ ነው ትራምፕ የተናገሩት።
More Stories
እንግሊዝን ያስቆጣው የኢራን ጥቃት
በሸካ ዞን ቴፒ ከተማ በሌማት ትሩፋት መርሐግብር የተሠማሩ ወጣቶች ተጠቃሚ እየሆኑ መምጣቸው ተገለጸ።
ኢራን ላይ እየተካሄደ የሚገኘው ወታደራዊ ዘመቻ …