በአሜሪካ አሪዞና ግዛት ስኮትስዴል አውሮፕላን ማረፊያ ውስጥ የሞትሊ ክሩይ ባንድ ሙዚቀኛ ቪንስ ኒል ንብረት የሆነ የግል አውሮፕላን ቆሞ ከነበረ ሌላ የቢዝነስ ጀት ጋር በመጋጨቱ የአንድ ሰው ህይወት ሲያልፍ በሌሎች ላይ ጉዳት መድረሱ ተገለፀ።
ሊያርፍ የነበረው ሌርጀት 35 ኤ የተባለ አነስተኛ የግል አውሮፕላን መንገዱን ስቶ ከሌላ ቆሞ ከነበረ ገልፍ ስትሪም 200 ከተባለ የቢዝነስ ጀት ጋር በመጋጨቱ ነው አደጋው የደረሰው፡፡
የስኮትስዴል ከተማ የእሳት አደጋ መከላከያ ቃል አቀባይ ዴቭ ሮሊዮ፤ በአደጋው የ 1 ሰው ህይወት ማለፉን በ4 ሰዎች ላይ ደግሞ ከባድ እና ቀላል ጉዳት መድረሱን ገልጸዋል፡፡
በዚህም የግል አውሮፕላኗን ሲያበር የነበረው ፓይለት በአደጋው ህይወቱ ማለፉ ነው የተሰማው ፡፡
የአውሮፕላኗ ባለቤት የሆነው ሙዚቀኛው ቪንስ ኒል በአውሮፕላኗ አለመሳፈሩን እና የሙዚቀኛው የፍቅር አጋር የሆነች ሴት በአደጋው ጉዳት እንደደረሰባት ተነግሯል፡፡
የአሜሪካ የፌዴራል አቬሽን አስተዳደር አውሮፕላኑ እንዴት መስመሩን ስቶ ከሌላ አውሮፕላን ጋር እንደተጋጨ እያጣራ መሆኑን ገልጿል፡፡
እንደ ሮይተርስ ዘገባ አደጋው የተከሰተው የአሜሪካ የአየር ደህንነት ከፍተኛ ምርመራ እየተደረገበት ባለበት ወቅት ነው ተብሏል፡፡
አሜሪካ በቅርብ ሳምንታት ውስጥ በዋሽንግተን ዲሲ፣ በፊላደልፊያ እንዲሁም በአላስካ በደረሱ የአቬሽን አደጋዎች በርካታ ሰዎች ህወታቸውን አጥተዋል፡፡
More Stories
ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከዳያስፖራው ማህበረሰብ አጀንዳ ማሰባሰብ ጀመረ
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክር ቤት የዘርፍ ቋሚ ኮሚቴዎች የ2017 በጀት አመት የአስፈፃሚ አካላት አፈፃፀም ግምገማ መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።
ማህበረሰቡ በከባድ ዝናብ ምክንያት ከሚከሰቱ አደጋዎች እንዲጠነቀቅ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አሳሰበ።