የዩክሬን ፕሬዝዳንት ቮለድሚር ዘለንስኪ የሩሲያ እና የዩክሬን ጦርነት ለማቆም ከሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ጋር በድርድር ጠረጴዛ ላይ ለመቀመጥ ዝግጁ መሆናቸውን ተናግረዋል ።
ፕሬዝዳንቱ ከፒርስ ሞርጋን ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ ፑቲንን እንደ “ጠላት” እንደሚመለከቷቸው ገልጸው ነገር ግን “ለዩክሬን ህዝብ ሰላም የሚያመጣ ከሆነ ቀጥተኛ ድርድር ለማድረግ ዝግጁ ነኝ” ብለዋል፡፡
በድርድሩ ላይ ከሁለቱ ፕሬዝዳንቶች ባለፈ አራት ታዛቢዎች እንዲሳተፉ እንደሚፈልጉ የገለጹት ፕሬዝዳንቱ ማንነታቸውን በይፋ ከመናገር ተቆጥበዋል፡፡
More Stories
በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ከ34 ሺህ በላይ ተማሪዎች የምገባ መርሐ ግብር ተጠቃሚ ሆነዋል
የፕሬዝዳንቶቹ የስልክ ውይይት
በሸካ ዞን ማሻ ወረዳ የበልግ የአረንጓዴ አሻራ በወረዳ ደረጃ የማስጀመሪያ ፕሮግራም ተካሄዷል ።