አሁን ላይ ከእንሰት ተክል አስተዋፅኦዎ ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ በመምጣቱ ምክንያት በዘርፉ ጥናትና ምርምሮች እየተከናወኑ መሆናቸውን መረጃዎች ያመላክታሉ።
በዚህም እንሰት ለምግብነትና ለተለያዩ የቤት ቁሳቁስ ሆኖ ከመዋል አልፎ ተረፈ ምርቱ በፋብሪካ ውስጥ ገቢቶ ውጤታማ ስራዎች እየተሰሩ መሆናቸው የቅርብ ጊዜ ትውስታ በመሆኑ ለዘርፉ ከፍተኛ ትኩረት ተስጥቶ እየተሰራ ይገኛል።
የአንድራቻ ወረዳ እርሻ፣ደን፣አከባቢ ጥበቃና ህብረት ስራ ፅ/ቤት በበጀት ዓመቱ 12 ሚሚልዮን የእንሰት ችግኝ ለመትከል ቅድመ ዝግጂት እያደረገ እንደሚገኝ የገለጹት የጽ/ቤቱ ኃላፊ አቶ አክሊሉ ሸነኖ ከባለፈው አመት ጀምሮ የችግኝ ዝግጅት እንዲደረግ ከአርሶ አደሮች ጋር በመግባባት ሰፋፍ ስራዎች ስሰሩ መቆየቱን አመላክተዋል።
በተያዘው አመት የተጣለውን ግብ ለማሳካት በየደረጃው የሚገኙ ባለድርሻ አካላት ልደግፉና በጋራ መስራት እንደሚገባም ጽ/ቤቱ አሳስበዋል።
More Stories
ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከዳያስፖራው ማህበረሰብ አጀንዳ ማሰባሰብ ጀመረ
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክር ቤት የዘርፍ ቋሚ ኮሚቴዎች የ2017 በጀት አመት የአስፈፃሚ አካላት አፈፃፀም ግምገማ መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።
ማህበረሰቡ በከባድ ዝናብ ምክንያት ከሚከሰቱ አደጋዎች እንዲጠነቀቅ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አሳሰበ።