ማሻ፣ ጥር 5፣ 2017 (ደሬቴድ ማሻ ቅርንጫፍ) የሩሲያ የመከላከያ ሚኒስቴር ሁለት ተጨማሪ የዩክሬን መንደሮችን መቆጣጠሩን አስታውቋል፡፡
መንደሮቹ በምስራቅ ዶኔትስክ ግዛት የምትገኘው ያንታርን እና የሰሜን ምስራቅ ካርኪቭ ግዛቷ ካሊኖቭ መሆናቸው ተመላክቷል፡፡
ጥቃቱ የዩክሬን ፕሬዚዳንት ቮሎድሚር ዘለንስኪ አጋሮቻቸው ወደ ኪየቭ ሊልኩ ቃል የገቡትን ጦር መሳሪያ እንዲያደርሱ መጠየቃቸውን ተከትሎ ነው የተፈጸመው ።
የሩሲያ መከላከያ ሚኒስቴር ወታደሮች ከኩራኮቭ በስተደቡብ ምዕራብ 10 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የምስራቃዊ ዶኔትስክ ግዛት የሆነችውን ያንታርን መንደር መያዙን አስታውቋል።
በተጨማሪም የሩሲያ ወታደሮች በሰሜን ምስራቅ ካርኪቭ አካባቢ የካሊኖቭን መንደር መያዛቸውን አመልክቷል፡፡
የክሊኖቭ መንደር በኦስኪል ወንዝ ምዕራባዊ ዳርቻ ላይ እንደምትገኝ አልጀዚራ በዘገባው አስፍሯል፡፡
የሩሲያ ሃይሎች ወንዙን ከተሻገሩ በኋላ በምዕራቡ ዳርቻ ድልድይ መስራታቸው የተገለጸ ሲሆን÷ ወንዙን ለመሻገርም ብዙ ጥረት ሲያደርጉ መቆየታቸው ተጠቁሟል፡፡
(ኤፍ ኤም ሲ)
More Stories
የአየር ጠባይ ትንበያ መረጃ የታላቁ ሕዳሴ ግድብ የውኃ ሙሌት በታቀደው መሠረት እንዲከናወን ድርሻውን ተውጥቷል – ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፋ(ዶ/ር)
መጪው የበጋ የአየር ጠባይ ወቅቱን ያልጠበቀ ዝናብ በሚኖርባቸው አካባቢዎች በደረሱ ሰብሎች ላይ ተጽዕኖ ሊያደርስ ይችላል ተባለ።
የአውሮፓ ህብረት ያወጣቸውን ደንቦች መሠረት በማድረግ የግብርና ምርቶች ከደን ጭፍጨፋ ነፃ ሆነው እንዲመረቱ ከማድረግ አንፃር የግብርና ባለሙያዎች ሚና የጎላ እንደሆነ ተገለፀ ።