ማሻ፣ ታሕሣሥ 19፣ 2017 (ደሬቴድ ማሻ ቅርንጫፍ) የሩሲያው ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን በአገሪቱ አየር ክልል ውስጥ የተከሰከሰው የአዘርባጃን አውሮፕላን ላይ ለደረሰው አሰቃቂ አደጋ ይቅርታ ጠየቁ።
የሀገሪቱን ፕሬዚዳንት ኢልሃም አሊዬቭን ይቅርታ የጠየቁት ፑቲን “አሳዛኝ ክስተት” ያሉት የአውሮፕላን መከስከስ በመፈጠሩ እና በአደጋው ምክንያት ለጠፋው የሰው ህይወት የተሰማቸውን ሀዘን ገልጸዋል።
ጉዳት ለደረሰባቸው ሰዎችም በቶሎ እንዲያገግሙ ምኞታቸውን ገልጸዋል።
ክሬምሊን ባወጣው መግለጫ በአካባቢው ጥቃት በመፈጸም ላይ የነበሩ የዩክሬን ሰው አልባ አውሮፕላኖች ላይ የሩሲያ አየር መከላከያ ጥቃቱን የመከላከል ስራ አየሰራ እንደነበር መግለጹን አሶሼትድ ፕሬስ በዘገባው አስነብቧል፡፡
ይሁን እንጂ የአዘርባጃኑ አውሮፕላን በስህተት በሩሲያ የአየር መከላከያ ኃይል ተመትቶ ይሁን አይሁን ተገለጸ ነገር የለም።
62 መንገደኞችንና አምስት ሠራተኞችን ያሳፈረ የአዘርባጃን አየር መንገድ ንብረት የሆነው አውሮፕላን በካዛኪስታን አክታው ከተማ አቅራቢያ ባሳለፍነው ረቡዕ ተከስክሶ የ38 ሰዎች ህይወት ማለፉ ይታወሳል።
ምንጭ ከኤፍ ኤም ሲ ነው
More Stories
ብልጽግና በሃሳብ የበላይነት የሚያምን ፓርቲ ነው ፦ አቶ ሰብስቤ ሻዎኖ
የአየር ጠባይ ትንበያ መረጃ የታላቁ ሕዳሴ ግድብ የውኃ ሙሌት በታቀደው መሠረት እንዲከናወን ድርሻውን ተውጥቷል – ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፋ(ዶ/ር)
መጪው የበጋ የአየር ጠባይ ወቅቱን ያልጠበቀ ዝናብ በሚኖርባቸው አካባቢዎች በደረሱ ሰብሎች ላይ ተጽዕኖ ሊያደርስ ይችላል ተባለ።