ማሻ፣ ታሕሣሥ 8፣ 2017 (ደሬቴድ ማሻ ቅርንጫፍ) የሩሲያ ኑክሌር፣ ራዲዬሽንና ኬሚካል ጥበቃ ኃይል ዋና ኃላፊ ሌተናንት ጀነራል ኢጎር ኪሪሎቭ እና እረዳታቸው በተጠመደ ፈንጂ ምክንያት ሞስኮ ውስጥ ሕይወታቸው ማለፉ ተሰምቷል፡፡
ኃላፊው እና እረዳታቸው ሕይወታቸው ያለፈው ሞስኮ በሚገኘው መኖሪያ ቤታቸው አቅራቢያ በስኩተር ላይ በተጠመደ ፈንጂ መሆኑን የሀገሪቱ መርማሪ ኮሚቴ አስታውቋል።
300 ግራም የሚመዝነው ፈንጂ በርቀት መቆጣጠሪያ አማካኝነት መፈንዳቱን ዩሮኒውስ ዘግቧል፡፡
ሌተናንት ጄነራሉ የተከለከለ ኬሚካል በዩክሬን ጦርነት ጥቅም ላይ እንዲውል ፈቅደዋል በሚል ዩክሬን ትናንት መክሰሷ ይታወሳል፡
More Stories
ብልጽግና በሃሳብ የበላይነት የሚያምን ፓርቲ ነው ፦ አቶ ሰብስቤ ሻዎኖ
በቀጣዮቹ ቀናት በበርካታ አካባቢዎች የክረምቱ ዝናብ ተጠናክሮ ይቀጥላል
በአዕምሮ የበለጸገ ትውልድ እንዲፈጠር የምግብ -ስርዓትና ስርዓተ – ምግብ ትግበራዎችን በቅንጅት መምራት እንደሚገባ ተገለጸ