ማሻ፣ ታሕሣሥ 8፣ 2017 (ደሬቴድ ማሻ ቅርንጫፍ) የሩሲያ ኑክሌር፣ ራዲዬሽንና ኬሚካል ጥበቃ ኃይል ዋና ኃላፊ ሌተናንት ጀነራል ኢጎር ኪሪሎቭ እና እረዳታቸው በተጠመደ ፈንጂ ምክንያት ሞስኮ ውስጥ ሕይወታቸው ማለፉ ተሰምቷል፡፡
ኃላፊው እና እረዳታቸው ሕይወታቸው ያለፈው ሞስኮ በሚገኘው መኖሪያ ቤታቸው አቅራቢያ በስኩተር ላይ በተጠመደ ፈንጂ መሆኑን የሀገሪቱ መርማሪ ኮሚቴ አስታውቋል።
300 ግራም የሚመዝነው ፈንጂ በርቀት መቆጣጠሪያ አማካኝነት መፈንዳቱን ዩሮኒውስ ዘግቧል፡፡
ሌተናንት ጄነራሉ የተከለከለ ኬሚካል በዩክሬን ጦርነት ጥቅም ላይ እንዲውል ፈቅደዋል በሚል ዩክሬን ትናንት መክሰሷ ይታወሳል፡
More Stories
ከባድ የውንብድና እና የግድያ ወንጀል የፈፀሙ ሁለት ግለሰቦችን በቁጥጥር ስር በማዋል በእስራት ማስቀጣቱን የሸካ ዞን ፖሊስ አስታወቀ፡፡
በክልሉ ባለፉት ዘጠኝ ወራት ሙስናን ለመከላከል በተደረገው ጥረት ከ85 ሚሊዮን በላይ ብር የህዝብ ሃብት ማዳን ተችላል
ኢትዮጵያ እና ኢንግሊዝ በኢንቨስትመንት፣ በንግድ እና ኢኮኖሚ ያላቸውን ትብብር ለማሳደግ ተስማሙ