የሸካ ዞን ከተማ ልማትና የኮንስትራክሽን መምሪያ ምክትል ኃላፊ አቶ ካዳኔ ከስቶ እንደገለጹት ህንፃው በ2008 ዓ /ም ተጀምሮ በአከባቢው በተፈጠረው የጸጥታ ችግር ግንባታው ዘጠኝ አመታትን የፈጀ መሆኑን ገልፀዋል።
ለግንባታው ወጪ ከ18 ሚሊዮን 7 መቶ ሺህ ብር በላይ ወጥቶለት መገንባቱ ተገልጸዋል።
የሸካ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት አቶ በላቸው ጀመረ በበኩላቸው ህንፃው መገንባቱ የፍርድ ቤቱን አገልግሎትን ቀልጣፋ ለማድረግ ሚናው የጎላ መሆኑን ተናግረዋል።
ለህንጻው ግንባታው መጓተት የፋይናንስ እጥረትና በአካባቢው የተፈጠረ የጸጥታ ችግር ተጽዕኖ መፍጠሩን ኘሬዝዳንቱ ገልጸዋል።
ግንባታውን ያከናወነው የአልሳም ኮንስራክሽን ስራ አስኪያጅ ኢኒጂነር ጀማል አሊ ህንጻው በተለያዩ ምክንያቶች የተጓተተ ቢሆንም አሁን ላይ ተጠናቋል ለአገልግሎት በቅቷል ሲሉ በርክክቡ ወቅት ገልጸዋል።
በህንጻው ርክክብ ላይ የተገኙት የሸካ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አበበ ማሞ እንደተናገሩት የተጀመሩት ግንባታዎች መጠናቀቃቸው ለዞኑ የሚያበረክተው አስተዋፆ ከፍተኛ መሆኑን ተናግረው ለህዝብ ጥራትና ቀልጣፋ አገልግሎት ለመስጠት ሚናው የጎ ነው ብለዋል።
የትኛውም ልማት በመተጋገዝና በመተባበር እንዲሁም አንዱ የጀመረውን አንደኛው የማጠናቀቅ ተግባር የዱላ ቅብብሎሽ ስራ በመሆኑ በቀጣይም ተጠናክሮ መቀጥል አለበት ብለዋል።
More Stories
ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከዳያስፖራው ማህበረሰብ አጀንዳ ማሰባሰብ ጀመረ
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክር ቤት የዘርፍ ቋሚ ኮሚቴዎች የ2017 በጀት አመት የአስፈፃሚ አካላት አፈፃፀም ግምገማ መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።
ማህበረሰቡ በከባድ ዝናብ ምክንያት ከሚከሰቱ አደጋዎች እንዲጠነቀቅ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አሳሰበ።