የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነብያት ጌታቸው በወቅታዊ እና ዓለም አቀፋዊ ጉዳዮች ዙሪያ ለመገናኛ ብዙኃን መግለጫ ሰጥተዋል። በመግለጫቸውም፤ የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ታየ አጽቀሥላሴ ባለፉት ሁለት ቀናት ውስጥ የ24 አገራት አዲስ አምባሳደሮችን የሹመት ደብዳቤ በጽ/ቤታቸው መቀበላቸውን ተናግረዋል። በሥነ ሥርዓቱ ላይ አምባሳደሮቹ አገሮቻቸው ከኢትዮጵያ ጋር ያላቸውን የሁለትዮሽ ግንኙነት የበለጠ ለማጠናከር በቆይታቸው እንደሚሰሩ ማረጋገጣቸውን አምባሳደር ነብያት ገልጸዋል። ቃል አቀባዩ በኢትዮጵያ አዲስ ኤምባሲ የከፈቱ አገራት አምባሳደሮችም የሹመት ደብዳቤያቸውን ለፕሬዝዳንቱ ማቅርባቸውን እና ለአብነት ያህል ስሎቬኒያ አምባሳደር ተጠቃሽ መሆናቸውን አንስተዋል።
EBC
More Stories
ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከዳያስፖራው ማህበረሰብ አጀንዳ ማሰባሰብ ጀመረ
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክር ቤት የዘርፍ ቋሚ ኮሚቴዎች የ2017 በጀት አመት የአስፈፃሚ አካላት አፈፃፀም ግምገማ መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።
ማህበረሰቡ በከባድ ዝናብ ምክንያት ከሚከሰቱ አደጋዎች እንዲጠነቀቅ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አሳሰበ።