የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነብያት ጌታቸው በወቅታዊ እና ዓለም አቀፋዊ ጉዳዮች ዙሪያ ለመገናኛ ብዙኃን መግለጫ ሰጥተዋል። በመግለጫቸውም፤ የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ታየ አጽቀሥላሴ ባለፉት ሁለት ቀናት ውስጥ የ24 አገራት አዲስ አምባሳደሮችን የሹመት ደብዳቤ በጽ/ቤታቸው መቀበላቸውን ተናግረዋል። በሥነ ሥርዓቱ ላይ አምባሳደሮቹ አገሮቻቸው ከኢትዮጵያ ጋር ያላቸውን የሁለትዮሽ ግንኙነት የበለጠ ለማጠናከር በቆይታቸው እንደሚሰሩ ማረጋገጣቸውን አምባሳደር ነብያት ገልጸዋል። ቃል አቀባዩ በኢትዮጵያ አዲስ ኤምባሲ የከፈቱ አገራት አምባሳደሮችም የሹመት ደብዳቤያቸውን ለፕሬዝዳንቱ ማቅርባቸውን እና ለአብነት ያህል ስሎቬኒያ አምባሳደር ተጠቃሽ መሆናቸውን አንስተዋል።
EBC
More Stories
ዜጎች በመልዕክት መላላኪያ አማራጮች በሚፈጸሙ የሳይበር ጥቃቶች ተጋላጭ እንዳይሆኑ ጥንቃቄ ማድረግ ይኖርባቸዋል፡-የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር
በሸካ ዞን አስተማማኝና ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥ እና የህግ የበላይነትን ለማስከበር ያለመ ዞናዊ የፀጥታ ግብረ ኃይል የምክክር መድረክ በቴፒ ከተማ ተካሄደ
ክልላዊ የተቀናጀ የማኅበረሰብ አቀፍ ተፋሰስ ልማት ማብሰሪያ ፕሮግራም በመካሄድ ላይ ይገኛል።