በጉባዔው መክፈቻ ላይ የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አሕመድ ሽዴ ባደረጉት ንግግር፤ የኢትዮጵያ እና ቻይና ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ እየተሸጋገር መሆኑን ገልጸዋል። ሚኒስትሩ ኢትዮጵያ በጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ አመራር ሁለንተናዊ የኢኮኖሚ ማሻሻያ ማድረጓን በመግለጽ፤ በዚህም ምቹ የኢንቨስትመንት ዕድል መፈጠሩን ተናግረዋል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ምስጋኑ አርጋ ባደረጉት ንግግር የኢትዮ-ቻይና ግንኙነት በሁኔታዎች የማይለወጥ ስትራቴጂክ አጋርነት መድረሱን እና የዛሬው ጉባዔም በኢኮኖሚ ዲፕሎማሲ ወደ አዲስ ምዕራፍ የሚያሸጋግር መሆኑን ገልጸዋል።
#EBC
More Stories
ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከዳያስፖራው ማህበረሰብ አጀንዳ ማሰባሰብ ጀመረ
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክር ቤት የዘርፍ ቋሚ ኮሚቴዎች የ2017 በጀት አመት የአስፈፃሚ አካላት አፈፃፀም ግምገማ መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።
ማህበረሰቡ በከባድ ዝናብ ምክንያት ከሚከሰቱ አደጋዎች እንዲጠነቀቅ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አሳሰበ።