በጉባዔው መክፈቻ ላይ የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አሕመድ ሽዴ ባደረጉት ንግግር፤ የኢትዮጵያ እና ቻይና ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ እየተሸጋገር መሆኑን ገልጸዋል። ሚኒስትሩ ኢትዮጵያ በጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ አመራር ሁለንተናዊ የኢኮኖሚ ማሻሻያ ማድረጓን በመግለጽ፤ በዚህም ምቹ የኢንቨስትመንት ዕድል መፈጠሩን ተናግረዋል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ምስጋኑ አርጋ ባደረጉት ንግግር የኢትዮ-ቻይና ግንኙነት በሁኔታዎች የማይለወጥ ስትራቴጂክ አጋርነት መድረሱን እና የዛሬው ጉባዔም በኢኮኖሚ ዲፕሎማሲ ወደ አዲስ ምዕራፍ የሚያሸጋግር መሆኑን ገልጸዋል።
#EBC
More Stories
ዜጎች በመልዕክት መላላኪያ አማራጮች በሚፈጸሙ የሳይበር ጥቃቶች ተጋላጭ እንዳይሆኑ ጥንቃቄ ማድረግ ይኖርባቸዋል፡-የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር
በሸካ ዞን አስተማማኝና ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥ እና የህግ የበላይነትን ለማስከበር ያለመ ዞናዊ የፀጥታ ግብረ ኃይል የምክክር መድረክ በቴፒ ከተማ ተካሄደ
ክልላዊ የተቀናጀ የማኅበረሰብ አቀፍ ተፋሰስ ልማት ማብሰሪያ ፕሮግራም በመካሄድ ላይ ይገኛል።