በጉባዔው መክፈቻ ላይ የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አሕመድ ሽዴ ባደረጉት ንግግር፤ የኢትዮጵያ እና ቻይና ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ እየተሸጋገር መሆኑን ገልጸዋል። ሚኒስትሩ ኢትዮጵያ በጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ አመራር ሁለንተናዊ የኢኮኖሚ ማሻሻያ ማድረጓን በመግለጽ፤ በዚህም ምቹ የኢንቨስትመንት ዕድል መፈጠሩን ተናግረዋል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ምስጋኑ አርጋ ባደረጉት ንግግር የኢትዮ-ቻይና ግንኙነት በሁኔታዎች የማይለወጥ ስትራቴጂክ አጋርነት መድረሱን እና የዛሬው ጉባዔም በኢኮኖሚ ዲፕሎማሲ ወደ አዲስ ምዕራፍ የሚያሸጋግር መሆኑን ገልጸዋል።
#EBC
More Stories
መንግስት በፈጠራና ክህሎት ላይ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ነው – ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ
ሀገራዊ የጤና ፖሊሲ ከመከላከልባሻገር አክሞ መዳንን መሰረት ያደረገ ስራን መስራት እንደሚገባ ተገለፀ።
በኢራን ወደብ በደረሰ ፍንዳታ 25 ሰዎች ህይወታቸው አለፈ