ከሳምንታት በፊት በተካሄደው የቺካጎ ማራቶን የዓለማችን ፈጣኑን የማራቶን ሰዓት ያስመዘገበችው ኬንያዊቷ አትሌት ሩት ቼፕንጌቲች በአፍሪካ ትልቁ የጎዳና ውድድር ላይ በክብር እንግድነት ለመታደም በሚቀጥለው ሳምንት ወደ አዲስ አበባ ትገባለች። “ወደ ኢትዮጵያ ልመጣ በመሆኔ በጣም ደስ ብሎኛል” ስትል ሩት የታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ውድድር አዘጋጆች ጋር ባደረገችው ቃለ ምልልስ ተናግራለች። “በእንግድነት ወደ ኢትዮጵያ በመምጣቴ ክብር ይሰማኛል እናም ኃይሌን ጨምሮ ሌሎች ታዋቂ አትሌቶችን ለማግኘት ጓጉቻለሁ” ብላለች፡፡ ቼፕንጌቲች ባለፈው ወር በቺካጎ ሶስተኛ የማራቶን ሻምፒዮን በመሆን 2 ሰአት ከ9 ደቂቃ ከ56 ሰከንድ አዲስ የአለም ክብረወሰን አስመዝግባለች። በዚህም በኢትዮጵያዊቷ ትግስት አሰፋ ተይዞ የነበረውን ክብረወሰን ከሁለት ደቂቃ በታች በማሻሻል አጠናቃለች።
EBC
More Stories
የሸካ ዞን የታዳጊ ወጣቶች የእግርኳስ ቡድን የ2018 ክልል አቀፍ ውድድር የዋንጫ አሸናፊ ሆነ።
5ተኛው የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የባህል ስፖርቶች ውድድር፣ የባህል ፌስቲቫል እና የታዳጊ ወጣቶች ምዘና ውድድር የታለመውን ግብ ያሳካ መሆኑ ተገለጸ።
ባካሪ ሳኛ ኢትዮጵያ ገባ