
ኪም ጆንግ ኡን የሁለቱን ኮሪያዎች መሪዎች ያጨባበጡት ዶናልድ ትራምፕ ወደ ስልጣን እንዲመጡ ፍላጎት እንዳላቸው ተነግሯልአሜሪካ 47ኛ ፕሬዝዳንታዊ ምርጫዋን በምታደርግበት በዛሬው እለት ሰሜን ኮሪያ በርካታ ባለስቲክ ሚሳኤሎችን አስወንጭፋለች።የጃፓን የመከላከያ ሚኒስትር ጄን ናካታኒ እንደገለጹት ፒዮንግያንግ በጥቂቱ ሰባት አጭር ርቀት የሚምዘገዘጉ ሚሳኤሎችን ተኩሳለች።ሚሳኢሎቹ በ100 ኪሎሜትር ከፍታ እስከ 400 ኪሎሜትሮች መምዘግዘጋቸውንና በኮሪያ ልሳነ ምድር እና በጃፓን መካከል በሚገኝ ውሃማ ስፍራ መውደቃቸውንም ነው ሚኒስትሩ ያስታወቁት።የደቡብ ኮሪያ መከላከያ ሚኒስቴርም ጎረቤት ሰሜን ኮሪያ የሴኡልን ወታደራዊ ተቋማትና በሀገሪቱ የሚገኘውን የአሜሪካ የጦር ሰፈር ሊይጠቁ የሚችሉ ሚሳኤሎችን ማስወንጨፏን ገልጿል።ፒዮንግያንግ የዛሬውን የሚሳኤል ሙከራ ያደረገችው ኪም ጆንግ ኡን አሜሪካ ድረስ ሊምዘገዘግ የሚችል “ሃውሶንግ-19” የተሰኘ አህጉር አቋራጭ ባለስቲክ ሚሳኤል ባስወነጨፈች በቀናት ልዩነት ነው።በሙከራው የተበሳጩት አሜሪካ፣ ደቡብ ኮሪያ እና ጃፓንም ባለፈው እሁድ ግዙፍ የሶስትዮሽ የአየር ልምምድ ማድረጋቸው ይታወሳል።
Al-Ain
More Stories
ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከዳያስፖራው ማህበረሰብ አጀንዳ ማሰባሰብ ጀመረ
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክር ቤት የዘርፍ ቋሚ ኮሚቴዎች የ2017 በጀት አመት የአስፈፃሚ አካላት አፈፃፀም ግምገማ መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።
ማህበረሰቡ በከባድ ዝናብ ምክንያት ከሚከሰቱ አደጋዎች እንዲጠነቀቅ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አሳሰበ።