የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መሥተዳድር ሽመልስ አብዲሳ የ ‘ሆረ ፊንፊኔ’ ኢሬቻ በዓል በድምቀት እንዲከበር አስተዋጽዖ ያደረጉ አካላትን አመሰገኑ፡፡የ ‘ሆረ ፊንፊኔ’ ኢሬቻ በዓል በአዲስ አበባ ከተማ ዛሬ በድምቀት ተከብሯል፡፡ይህን ተከትሎም በዓሉን እሴቱን ጠብቆ በድምቀት እንዲከበር ያደረጉ አካላትን ማመስገናቸውን የኦሮሚያ ክልል ኮሙኒኬሽን ቢሮ መረጃ አመላክቷል፡፡በነገው ዕለትም በቢሾፍቱ ከተማ ‘ሆረ ሀርሰዲ’ እንደሚከበር ገልጸው÷ በዓሉ ዕሴቱን በጠበቀ ሁኔታ በድምቀት እንዲከበር ሁሉም የድርሻውን እንዲወጣ ጥሪ አቅረበዋል፡፡
EBC
More Stories
“እኔ በሕይወት እያለሁ መምህራን መኪና ኖሯቸው ከማየት በላይ የሚያስደስተኝ ነገር የለም”፦ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከሁሉም ክልሎች እና ከተማ አስተዳደሮች ከተወጣጡ የጥበቡ ማኅበረሰብ ተወካዮች ጋር ያካሄዱትን ውይይት ዛሬ ምሽት (ሰኔ 9) በኢቢሲ ሁሉም አማራጮች ከምሽቱ 2:30 ላይ ይከታተሉ።
በቀጣይ 90 ቀናት የተቀመጡ ዕቅዶችን በውጤታማነት በመፈጸም እመርታዊ ውጤት ለማስመዝገብ ርብርብ ማድረግ ይኖርብናል፦አቶ ፍቅሬ አማን