እስራኤል ባለፈው እሁድ በሆዴይዳህ ወደብ በፈጸመችው የአየር ጥቃት ስድስት ሰዎች መሞታቸውና ከ57 በላይ ሰዎች መቁሰላቸው ይታወሳልየየመኑ ሃውቲ በማዕከላዊ እስራኤል በምትገኘው የወደብ ከተማ ጃፋ ላይ የድሮን ጥቃት መፈጸሙን አስታወቀ።የሃውቲ ቃል አቀባይ ያህያ ሳሬ በዛሬው እለት በሰጡት መግለጫ የቡድኑ ድሮኖችን ኢላማቸውን መምታታቸውን ተናግረዋል።የሃውቲ ድሮኖች “ከእስራኤል የራዳር እይታ ውጭ በመሆን እና ሳይመቱ የጠላትን ወሳኝ ኢላማዎች መተዋል” ማለታቸውንም ሬውተርስ ዘግቧል።ቡድኑ በቴል አቪቭ ላይም ተመሳሳይ የድሮን ጥቃት መፈጸሙን ያነሱት ቃል አቀባዩ፥ ተመተዋል ስለተባሉት ኢላማዎች ግን ዝርዝር መረጃን ከመስጠት ተቆጥበዋል።በትናንትናው እለት “ቁድስ 5” በተሰኘው ሮኬት እስራኤልን አጥቅተናል ያሉት ያህሳ ሳሪ፥ ቴል አቪቭ በጋዛ እና ሊባኖስ የጀመረችውን ጦርነት
AL-AIN
More Stories
“የኢራንን ሉዓላዊነት እስከመጨረሻው እስትንፋሳችን እናስጠብቃለን!” – የኢራን ጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም
በሕንድ የአውሮፕን መከስከስ አደጋ ሕይወታቸውን ያጡ የአንድ ቤተሰብ አባላት …
ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በ12 ሀገራት ላይ የጣሉት የጉዞ እገዳ ተግባራዊ ሆነ