በሊባኖስ የኢትዮጵያ ቆንስል ጄነራል ጽሕፈት ቤት ባወጣው መግለጫ÷ በሊባኖስ በተከሰተው ጦርነት ምክንያት ወደ ሀገራቸው መመለስ የሚፈልጉ ዜጎች ከሊባኖስ መውጣት የሚችሉበትን መንገድ እያመቻቸ መሆኑን አስታውቋል፡፡በዚሁ መሠረት ወደ ኢትዮጵያ ለመመለስ የሚፈልጉ እና እስከ አሁን ያልተመዘገቡ ወገኖች አስፈላጊውን መረጃ በማዘጋጀት እንዲመዘገቡ ጥሪ ቀርቧል፡፡ለምዝገባ አስፈላጊ የሆኑት መረጃዎችም÷ ሙሉ ስም ከነአያት(ፓስፓርት ላይ እንደተፃፈው)፣ የፓስፖርት ቁጥር፣ በሊባኖስ የቆይታ ጊዜ፣ የሊባኖስ ስልክ ቁጥር መሆናቸውን ጽሕፈት ቤቱ አስታውቋል፡፡ለምዝገባ የተዘጋጁት ስልክ ቁጥሮችም÷ 03-29-89-78፣ 76-03-08-23፣ 81-99-46-34፣ 70-29-80-91፣ 81-80-25-18፣ 70-84-25-24 እና 81-09-27-46 መሆናቸውን የጽሕፈት ቤቱ መረጃ አመላክቷል፡፡ጽሕፈት ቤቱ ቀደም ሲያል ያቀረበውን ጥሪ ተከትሎ የተመዘገቡና መመዝገባቸውን ያረጋገጡ ወገኖች በድጋሚ እንዳይመዘገቡ አሳስቧል፡፡
በሊባኖስ በተከሰተው ውጥረት ምክንያት ኢትዮጵያውያን ጉዳት እንዳይደርስባቸው ወደ ሀገራቸው እንዲመለሱ ለማድረግ ምዝገባ እንዲያከናውኑ ጥሪ ቀረበ፡፡

More Stories
“እኔ በሕይወት እያለሁ መምህራን መኪና ኖሯቸው ከማየት በላይ የሚያስደስተኝ ነገር የለም”፦ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከሁሉም ክልሎች እና ከተማ አስተዳደሮች ከተወጣጡ የጥበቡ ማኅበረሰብ ተወካዮች ጋር ያካሄዱትን ውይይት ዛሬ ምሽት (ሰኔ 9) በኢቢሲ ሁሉም አማራጮች ከምሽቱ 2:30 ላይ ይከታተሉ።
በቀጣይ 90 ቀናት የተቀመጡ ዕቅዶችን በውጤታማነት በመፈጸም እመርታዊ ውጤት ለማስመዝገብ ርብርብ ማድረግ ይኖርብናል፦አቶ ፍቅሬ አማን