በሊባኖስ በመሸገው ሂዝቦላህ ላይ የሚወሰደው ሁለንተናዊ እርምጃ ተጠናክሮ መቀጠሉን የእስራኤል መከላከያ ሰራዊት ገልጿል፡፡በዛሬው ዕለትም በቤሩት በተመረጡ የሂዝቦላህ ይዞታዎች ላይ የተሳካ የአየር ላይ ጥቃት መፈጸሙን ጦር ባወጣው መግለጫ አመላክቷል፡፡በዚህም የሂዝቦላህ ደህንነት ሃላፊና የማዕከላዊ ም/ቤቱ ወሳኝ አባል ነቢል ኳዑክ መገደሉን ነው ያስታወቀው፡፡ በአንጻሩ በከፍተኛ አመራሩ መገደል ዙሪያ ሂዝቦላህ ያለው ነገር አለመኖሩን ቢቢሲ በዘገባው አስፍሯል፡፡እስራኤል በሂዝቦላህ ላይ እየወሰደች ባለው ወታደራዊ እርምጃ የቡድኑን መሪ ሀሰን ነስራላህን ባሳለፍነው አርብ መግደሏ ይታወሳል፡፡
እስራኤል በሊባኖስ በፈጸመችው የአየር ላይ ጥቃት ተጨማሪ የሂዝቦላህ ከፍተኛ አመራር መግደሏን አስታውቃለች፡፡
More Stories
የአውሮፓ ህብረት ያወጣቸውን ደንቦች መሠረት በማድረግ የግብርና ምርቶች ከደን ጭፍጨፋ ነፃ ሆነው እንዲመረቱ ከማድረግ አንፃር የግብርና ባለሙያዎች ሚና የጎላ እንደሆነ ተገለፀ ።
ትራምፕ ቲክ ቶክን የሚገዙ የአሜሪካ ባለሀብቶች ማግኘታቸውን ገለፁ
ሩሲያ እና ህንድ በጦር መሳሪያ አቅርቦት ላይ ያላቸውን ትብብር ለማሳደግ እንደሚሰሩ አስታወቁ፡፡