በኒውዮርክ እየተካሄደ ከሚገኘው 79ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት (የተመድ) ጠቅላላ ጉባዔ ጎን ለጎን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አጽቀስላሴ ከኡጋንዳ እና ርዋንዳ አቻቸው ጋር ተወያይተዋል።አምባሳደር ታዬ ከኡጋንዳ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ኢሊቪየር ኑሁንጊሬሄ እና የርዋንዳ ውጭ ጉዳይ እና ዓለም አቀፍ ትብብር ሚኒስትር ጄጄ ኦዶንጎ ጋር በሁለትዮሽ ጉዳዮች ላይ መክረዋል።ከርዋንዳው ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጄጄ ኦዶንጋ ጋር በነበራቸው ውይይት በናይል የውሃ ሃብት ፍትሃዊ አጠቃቀም ላይ ሁለቱ ሀገራት ስላላቸው የጋራ አቋም ዙሪያ ሀሳብ ተለዋውጠዋል።ከኡጋንዳው አቻቸው ጋር በነበራቸው ውይይትም በምስራቅ አፍሪካ ቀጣና የሰላም ሁኔታ ላይ የመከሩ ሲሆን፤ በድህረ በሶማሊያ ከአፍሪካ ኅብረት የሽግግር ሰላም ማስከበር ተልዕኮ (አትሚስ) መደረግ ስላለባቸው ጥንቃቄዎች እና አጠቃላይ ሁኔታ ላይ ተወያይተዋል።ኢትዮጵያና ኡጋንዳ በሶማሊያ ሰራዊት አሰማርተው የነበሩ በመሆናቸው ድህረ አትሚስ ሽብርተኝነትን በመዋጋት የተመዘገበው ውጤት ወደኋላ በማይመልስ መልኩ መፈጸም እንዳለበት መክረዋል።በጥቅምት ወር አጋማሽ ላይ ኡጋንዳ የምታስተናግደው የናይል ጉባዔ የናይል ተፋሰስ የትብብር ማዕቀፍ ወደ ተግባር እንዲገባ የሚያስችሉ ውሳኔዎች የሚተላለፉበት እንደሚሆን ያላቸውን እምነት አምባሳደር ታዬ ገልጸዋል።
FBC
More Stories
ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከዳያስፖራው ማህበረሰብ አጀንዳ ማሰባሰብ ጀመረ
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክር ቤት የዘርፍ ቋሚ ኮሚቴዎች የ2017 በጀት አመት የአስፈፃሚ አካላት አፈፃፀም ግምገማ መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።
ማህበረሰቡ በከባድ ዝናብ ምክንያት ከሚከሰቱ አደጋዎች እንዲጠነቀቅ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አሳሰበ።