የካፌቾ ብሔረሰብ የቋንቋ እና የባህል ሲምፖዚየም በቦንጋ ከተማ እየተካሔደ ይገኛል፡፡ ሲምፖዚየሙ የብሔረሰቡን የዘመን መለወጫ በዓል ማሽቃሮ ምክንያት በማድረግ የተዘጋጀ ነው።የማሽቃሮ በዓል በቦንጋ ከተማ በነገው ዕለት ይከበራል።ማሽቃሮ የዘመን መለወጫ በዓል የክረምቱ ወቅት አልፎ ብርሃናማው ጊዜ መግባቱ የሚበሰርበት ነው።የእርቅ፣ የሰላም እና የአንድነት መገለጫ በሆነው ማሽቃሮ ቀጣዩ ጊዜ የፍቅር እና የልማት እንዲሆን ሁሉም የብሔረሰቡ አባት ምርቃት የሚያገኙበት እንደሆነም የአካባቢው የሀገር ሽማግሌዎች ተናግረዋል።
EBC
More Stories
ባለፉት ሦስት ዓመታት ለሰብዓዊ ድጋፍ በሚል የገባ ስንዴ የለም – አምባሳደር ሽፈራው ተክለማርያም (ዶ/ር)
በገጠሩ የሀገሪቱ አካባቢዎች መንግስት የሚዘረጋቸውን የተለያዩ ኢንሸቲቦችን ቀድሞና ፈጥኖ ተግባራዊ ከማድረግ አንፃር የተሻሉ አፈጻጸሞች መታየታቸው ተገለፀ ።
የሚኒስትሮች ምክር ቤት በ6 ጉዳዮች ላይ ውሳኔ አሳለፈ