ኢትዮጵያ በተባበሩት መንግሥታት ዓለም አቀፍ የኤሌክትሮኒክ መንግሥት መለኪያ ደረጃዋን አሻሻለች፡፡በየሁለት ዓመቱ የሚወጣው የተባበሩት መንግሥታት ዓለም አቀፋዊ የኢ-መንግሥት መለኪያ ትናንት በኒዮርክ ከመንግሥታቱ ስብሰባ ጎን ለጎን ይፋ ሆኗል።ይህ ዓለም አቀፋዊ የኤሌክትሮኒክ መንግሥት መለኪያ የዓለም ሀገራት በየሁለት ዓመቱ ከሌሎች ሀገራት አንጻር እና በራሳቸው ካሳዩት እድገት ጋር በማነጻጸር ሀገራቱ በዘርፉ ያደረጉትን መሻሻሎች ብሎም ያስመዘገቧቸውን ለውጦች የሚያሳይ ነው።በዓለም አቀፍ የኤሌክትሮኒክ መንግሥት ሪፖርት መሠረት ኢትዮጵያ ከነበረችበት 10 ደረጃዎችን ማሻሻል ችላለች፡፡
FBC
More Stories
ዜጎች በመልዕክት መላላኪያ አማራጮች በሚፈጸሙ የሳይበር ጥቃቶች ተጋላጭ እንዳይሆኑ ጥንቃቄ ማድረግ ይኖርባቸዋል፡-የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር
በሸካ ዞን አስተማማኝና ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥ እና የህግ የበላይነትን ለማስከበር ያለመ ዞናዊ የፀጥታ ግብረ ኃይል የምክክር መድረክ በቴፒ ከተማ ተካሄደ
ክልላዊ የተቀናጀ የማኅበረሰብ አቀፍ ተፋሰስ ልማት ማብሰሪያ ፕሮግራም በመካሄድ ላይ ይገኛል።