ኢትዮጵያ ለምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) ዘላቂ የቱሪዝም ፍኖተ ካርታ ትግበራ ግንባር ቀደም ሚናዋን እንደምትወጣ የቱሪዝም ሚኒስትር አምባሳደር ናሲሴ ጫሊ ተናገሩ።የኢጋድ አባል ሀገራት የቱሪዝም ሚኒስትሮች በቀጠናው ለቀጣይ አስርት ዓመታት ተግባር ላይ ይውላል በተባለው እና ነገ ይፋ በሚደረገው “የኢጋድ ዘላቂ የቱሪዝም ፍኖተካርታ” ላይ እየተወያዩ ነው።በውይይቱ መክፈቻ ላይ ንግግር ያደረጉት የቱሪዝም ሚኒስትር አምባሳደር ናሲሴ ጫሊ÷ በቀጠናው የዓለም አቀፍ ጎብኝዎችን ማሳደግ የሚያስችል አቅምን መፍጠር የሚያስችል ፍኖተ ካርታ እንደሆነ አንስተዋል።ለዚህም የጋራ ትብብርን በማሳደግ መልከ ብዙ ባህሎችን ለጎብኚዎች ማቅረብ ይገባል ብለዋል።ይህንንም እውን ለማድረግ እያንዳንዱ የቀጣናው አባል ሀገር በጋራ እና በተናጠል አቅማቸውን ሊጠቀሙ እንደሚገባም አንስተዋል።ለዚህም የቱሪስት ስነ ምህዳራዊ ምቹነትን የሚፈጥሩ መሰረተ ልማቶችን እና የተቋማት ማሻሻያዎችን በማድረግ እየተሰራ ነው ብለዋል።በምክክር መርሃ ግብሩ ላይ የኢጋድ ዋና ጸሃፊ ወርቅነህ ገበየሁ (ዶ/ር) እና የቀጣናው ሀገራት የቱሪዝም ሚኒስትሮች እየተሳተፉ ነው።
FBC
More Stories
ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከዳያስፖራው ማህበረሰብ አጀንዳ ማሰባሰብ ጀመረ
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክር ቤት የዘርፍ ቋሚ ኮሚቴዎች የ2017 በጀት አመት የአስፈፃሚ አካላት አፈፃፀም ግምገማ መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።
ማህበረሰቡ በከባድ ዝናብ ምክንያት ከሚከሰቱ አደጋዎች እንዲጠነቀቅ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አሳሰበ።