የጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ እና የሚኒስቴሩ የሥራ ኃላፊዎች ብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራምን ጎብኝተዋል። ሚኒስትሯ እና ኃላፊዎቹ ከፕሮግራሙ አመራሮች ጋር ባደረጉት ቆይታ፥ የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ከጤና ዘርፍ ጋር ስለሚኖረው ትሥሥር ተወያይተዋል። በቀጣይ ብሔራዊ መታወቂያ ለጤናው ዘርፍ በሚጠቅምበት ጉዳይ ላይ አብረው ለመሥራት የሚያስችላቸውን የመግባቢያ ስምምነትም ተፈራርመዋል።የሥራ ጉብኝት ያደረጉት የጤና ሚኒስትሯ እና የሥራ ኃላፊዎቹ ለፋይዳ መታወቂያ ምዝገባ ማድረጋቸውንም ከብሔራዊ መታወቂ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።
የጤና ሚኒስቴር እና ብሔራዊ መታወቂያ የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረሙ
More Stories
የአየር ጠባይ ትንበያ መረጃ የታላቁ ሕዳሴ ግድብ የውኃ ሙሌት በታቀደው መሠረት እንዲከናወን ድርሻውን ተውጥቷል – ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፋ(ዶ/ር)
መጪው የበጋ የአየር ጠባይ ወቅቱን ያልጠበቀ ዝናብ በሚኖርባቸው አካባቢዎች በደረሱ ሰብሎች ላይ ተጽዕኖ ሊያደርስ ይችላል ተባለ።
የወባ መከላከያ ክትባት በሽታውን ለማጥፋት በማለም ለተጀመረው ርብርብ ትልቅ እገዛ ያደርጋል አሉ የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ደረጄ ዱጉማ።