የጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ እና የሚኒስቴሩ የሥራ ኃላፊዎች ብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራምን ጎብኝተዋል። ሚኒስትሯ እና ኃላፊዎቹ ከፕሮግራሙ አመራሮች ጋር ባደረጉት ቆይታ፥ የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ከጤና ዘርፍ ጋር ስለሚኖረው ትሥሥር ተወያይተዋል። በቀጣይ ብሔራዊ መታወቂያ ለጤናው ዘርፍ በሚጠቅምበት ጉዳይ ላይ አብረው ለመሥራት የሚያስችላቸውን የመግባቢያ ስምምነትም ተፈራርመዋል።የሥራ ጉብኝት ያደረጉት የጤና ሚኒስትሯ እና የሥራ ኃላፊዎቹ ለፋይዳ መታወቂያ ምዝገባ ማድረጋቸውንም ከብሔራዊ መታወቂ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።
የጤና ሚኒስቴር እና ብሔራዊ መታወቂያ የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረሙ
More Stories
ዜጎች በመልዕክት መላላኪያ አማራጮች በሚፈጸሙ የሳይበር ጥቃቶች ተጋላጭ እንዳይሆኑ ጥንቃቄ ማድረግ ይኖርባቸዋል፡-የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር
በሸካ ዞን አስተማማኝና ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥ እና የህግ የበላይነትን ለማስከበር ያለመ ዞናዊ የፀጥታ ግብረ ኃይል የምክክር መድረክ በቴፒ ከተማ ተካሄደ
ክልላዊ የተቀናጀ የማኅበረሰብ አቀፍ ተፋሰስ ልማት ማብሰሪያ ፕሮግራም በመካሄድ ላይ ይገኛል።