ድጋፉን አስመልክቶ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት ያስተላለፋት የቴፒ ከተማ ከንቲባ አቶ ወንድሙ ግርማ ይህ ዓይነቱ ድጋፍ ቀጣይነት እንዲኖረዉ ይሰራል ብለዋል።በጎ ፈቃደኛ ግለሰቦችንና የተለያዩ ባለድርሻ አካላትን በማስተባበር 350 ለሚሆኑ ለተቸገሩ ወገኖች አዲሱን ዓመት ምክንያት በማድረግ ለእያንዳዳቸዉ የ 2 ሊትር ዘይትና የ4 ኪሎ ግራም ዱቄት ድጋፍ መበርከቱን የተናገሩት ደግሞ በቴፒ ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ጽህፈት ቤት የሴቶች ሊግ ሀላፊ ወይዘሮ ይጋርዱ ጤናዉ ናቸዉ። በተመሳሳይ በከተማዉ መዋቅር ዉስጥ የሚሰሩና ከ2 ሺህ ብር በታች የሚከፈላቸዉ 126 ደመወዝተኞችም ለእያንዳንዳቸዉ የ5 ሊትር ዘይት ድጋፍ ተሰጥቷቸዋል። ዘጋቢ ጌትነት ገረመዉ።
አዲሱን ዓመት ምክንያት በማድረግ 350 ለሚሆኑ በቴፒ ከተማ ለሚኖሩ አቅመ ደካማ ወገኖች የበዓል መዋያ ድጋፍ መበርከቱ ተገለጸ።

More Stories
መንግስት በፈጠራና ክህሎት ላይ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ነው – ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ
ሀገራዊ የጤና ፖሊሲ ከመከላከልባሻገር አክሞ መዳንን መሰረት ያደረገ ስራን መስራት እንደሚገባ ተገለፀ።
በኢራን ወደብ በደረሰ ፍንዳታ 25 ሰዎች ህይወታቸው አለፈ