የጃኮብ ዙማ ሴት ልጅ የኢስዋትኒ ንጉስ 16ኛዋ ሚስት በመሆን ተሞሸረችየጋብቻ ስነ ስርዓቱ ባሳለፍነው ሰኞ በኢስዋትኒ መዲና ሎባምባ ቤተ መንግስት ተካሂዷልአል-ዐይን 2024/9/5 15:22 GMTየቀድሞ የደቡብ አፍሪካ ፕሬዝዳንት ጃኮብ ዙማ ብዙ ሚስቶች ያሏቸው ሲሆን 20 ልጆችንም አፍርተዋልየጃኮብ ዙማ ሴት ልጅ የኢስዋትኒ ንጉስ 16ኛዋ ሚስት በመሆን ተሞሸረች፡፡ኖምችዶ ዙማ የ21 ዓመት እድሜ ያላት የቀድሞው የደቡብ አፍሪካ ፕሬዝዳንት ጃኮብ ዙማ ልጅም ናት፡፡የደቡብ አፍሪካ ጎረቤት የሆነችው የቀድሞዋ ስዋዚላንድ የአሁኗ ኢስዋትኒ ንጉሳዊ ስርዓት ያላት ሀገር ናት፡፡የፖለቲካ ፓርቲ ማቋቋም በህግ የከለከለችው ይህች ሀገር በንጉስ ምስዋቲ ሶስተኛ በመመራት ላይ ትገኛለች፡፡የ56 ዓመቱ የኢስዋትኒ ንጉስ የ21 ዓመቷን ኖምችዶ ዙማን 16ኛ ሚስት አድርገው ማግባታውን የሀገሪቱ ብዙሀን መገናኛዎች ዘግበዋል፡፡እንደ ዘገባዎቹ ከሆነ ጋብቻው 5 ሺህ ልጃገረዶች በተገኙበት ባህላዊ ስርዓቱን ጠብቆ ተካሂዷል፡፡
Al-Ain
More Stories
ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከዳያስፖራው ማህበረሰብ አጀንዳ ማሰባሰብ ጀመረ
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክር ቤት የዘርፍ ቋሚ ኮሚቴዎች የ2017 በጀት አመት የአስፈፃሚ አካላት አፈፃፀም ግምገማ መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።
ማህበረሰቡ በከባድ ዝናብ ምክንያት ከሚከሰቱ አደጋዎች እንዲጠነቀቅ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አሳሰበ።