ከቡርጀ ከሊፋ በቅርብ ርቀት እየተገነባ የሚገኘው “ቡርጀ አዚዚ” 725 ሜትር ቁመት ይኖረዋል ተብሏል ተከትሎ ሁለተኛው ሰማይ ጠቀስ ህንጻ እንደሚሆን በትናንትናው እለት ነው የተገለጸው።በ2024 ጥር ወር ቁፋሮው የተጀመረው “ቡርጅ አዚዚ” ከኤምሬትስ የሲቪል አቪየሽን ባለስልጣን እና ከሌሎች ተቋማት የሚሰጠው የግንባታ ፈቃድ ሲጠበቅ ቆይቷል።በዚህም ምን ያህል ፎቆች ያሉት ህንጻ እንደሚገነባ ሳይነገር ቆይቷል ።የአዚዚ ዴቨሎፕመንትስ መስራች ሚርዋይስ አዚዚ በትናንትናው እለት ግን ሲጠበቅ የነበረውን መረጃ አጋርተዋል። “ያቀረብነው ሁለት ዲዛይኖችን ነው ባለ526 እና 725 ሜትር ቁመት ህንጻ፤ ባለ725 ሜትሩ ህንጻ ዲዛይን ጸድቆልናል” ሲሉ ለዘናሽናል ኒውስ ተናግረዋል።ለሁለተኛውና ረጅሙ ህንጻ ዲዛይን ተጨማሪ የመሰረትና ቋሚ ግንባታዎችን ለማካሄድ አስቀድመን ተዘጋጅተናልም ነው ያሉት።
AL-AIN
More Stories
የአውሮፓ ህብረት ያወጣቸውን ደንቦች መሠረት በማድረግ የግብርና ምርቶች ከደን ጭፍጨፋ ነፃ ሆነው እንዲመረቱ ከማድረግ አንፃር የግብርና ባለሙያዎች ሚና የጎላ እንደሆነ ተገለፀ ።
ትራምፕ ቲክ ቶክን የሚገዙ የአሜሪካ ባለሀብቶች ማግኘታቸውን ገለፁ
ሩሲያ እና ህንድ በጦር መሳሪያ አቅርቦት ላይ ያላቸውን ትብብር ለማሳደግ እንደሚሰሩ አስታወቁ፡፡