በሥነጥበብ፣ በታሪክ እና በቅርስ ጠባቂነት፣ በንግግር አዋቂነት፣ በድርሰት ሥራዎቻቸው፣ በላቀ የምህድስን በሙያቸው እንዲሁም በበጎ አድራጊነት ሥራቸው ይታወቃሉ፡፡ ታታሪነትና እና ሀገርን መውደድ በተግባር ያሳዩን ሁለገብ ባለሙያ፣ ሁሉም በየዘርፉ እና በየአቅሙ ለሀገሩ ምን ማበርከት እንዳለበት ሠርተው ያሳዩ ሊቅ ናቸው፡፡ መኖሪያ ቤታቸው የኢትዮጵያ ባለውለታ የሆኑ ታላላቅ ሰዎችን በሚዘክሩ ታሪካዊ እና ዕድሜ ጠገብ ሥዕላት፣ ምስሎች እና ፎቶግራፎች፣ ቅርጻ ቅርጾች እንዲሁም የኢትዮጵያን ታሪክ እና ቅርስ በተመለከተ በጽሑፎች፣ በሰነድ፣ በምስል፣ በድምፅ እና በቪዲዮ ያሰባሰቧቸው መረጃዎችና ቅርሶች የተሞላ እንደሆነ የቅርብ ወዳጆቻቸው ይመሰክራሉ። ለኢትዮጵያ ታሪክ፣ ባህልና ቅርስ ያላቸው ክብር እና ተቆርቋሪነት እንዲሁም ለሕዝባቸው ያላቸው ፍቅር እናወገናዊነት በጣም ጥልቅ ነው ይባልላቸዋል።
EBC
More Stories
ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከዳያስፖራው ማህበረሰብ አጀንዳ ማሰባሰብ ጀመረ
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክር ቤት የዘርፍ ቋሚ ኮሚቴዎች የ2017 በጀት አመት የአስፈፃሚ አካላት አፈፃፀም ግምገማ መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።
ማህበረሰቡ በከባድ ዝናብ ምክንያት ከሚከሰቱ አደጋዎች እንዲጠነቀቅ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አሳሰበ።