ኢትዮጵያ ፈተናዎችን ተቋቁማ ፈጣን ዕድገት እያስመዘገበች መሆኗን የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አሕመድ ሽዴ ተናግረዋል፡፡ ኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንትን በመሳብ ረገድ በምስራቅ አፍሪካ ቀዳሚዋ ሀገር መሆኗንም አንስተዋል፡፡ ሀገሪቱ ያላት የካፒታል ገበያ፣ የተወሰዱ የኢኮኖሚ ማሻሻያዎች እና ሌሎች ሁኔታዎች፤ ለኢንቨስትመንት ተመራጭ እንደሚያደርጓትም ጠቁመዋል፡፡ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶ/ር) በበኩላቸው ሀገሪቱ የዲጂታል ኢኮኖሚን በመገንባት ሂደት ላይ መሆኗን መናገራቸውን ፋና ዘግቧል፡፡ የጤና ሚኒስትር ዶክተር መቅደስ ዳባ በበኩላቸው፤ በጤናው ዘርፍ ለመሰማራት የሚያስችሉ መሰረተ-ልማቶች የተሟሉ መሆናቸውን አመላክተዋል፡፡የኢትዮ-ቻይና ከፍተኛ የቢዝነስ ፎረም በቻይና ቤጂንግ በመካሄድ ላይ ይገኛል፡፡
EBC
More Stories
ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከዳያስፖራው ማህበረሰብ አጀንዳ ማሰባሰብ ጀመረ
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክር ቤት የዘርፍ ቋሚ ኮሚቴዎች የ2017 በጀት አመት የአስፈፃሚ አካላት አፈፃፀም ግምገማ መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።
ማህበረሰቡ በከባድ ዝናብ ምክንያት ከሚከሰቱ አደጋዎች እንዲጠነቀቅ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አሳሰበ።