ሰልፈኞቹ የኔታንያሁ አስተዳደር ቀሪዎቹን 101 ታጋቾች እንዲያስለቅቅ ጠይቀዋልበጋዛ ስድስት ታጋቾች መገደላቸውን ተከትሎ እስራኤላውያን ቁጣቸውን በአደባባይ እያሰሙ ነው።የኔታንያሁ አስተዳደር የተኩስ አቁም ስምምነት ላይ ደርሶ ታጋቾችን ማስለቀቅ አልቻለም ያሉ 500 ሺህ የሚገመቱ ሰልፈኞች በቴል አቪቭ፣ እየሩሳሌምና ሌሎች ከተሞች ድምጻቸውን አሰምተዋል።ሰልፈኞቹ በእየሩሳሌም መንገድ ዘግተው በጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ መኖሪያ ቤት ዙሪያ ተቃውሟቸውን ሲያሰሙ ውለዋል።የቴል አቪቭ ጎዳናዎችም የሟቾቹን ታጋቾች ምስሎች በያዙ ሰልፈኞች ተሞልተው መዋላቸውን ነው ሬውተርስ ያስነበበው።ሰልፈኞቹ የኔታንያሁ አስተዳደር ቀሪዎቹን 101 ታጋቾች ለማስለቀቅ በፍጥነት የተኩስ አቁም ስምምነት እንዲደርስ ጠይቀዋል።
Al-Ain
More Stories
ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከዳያስፖራው ማህበረሰብ አጀንዳ ማሰባሰብ ጀመረ
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክር ቤት የዘርፍ ቋሚ ኮሚቴዎች የ2017 በጀት አመት የአስፈፃሚ አካላት አፈፃፀም ግምገማ መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።
ማህበረሰቡ በከባድ ዝናብ ምክንያት ከሚከሰቱ አደጋዎች እንዲጠነቀቅ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አሳሰበ።