የአገልግሎቱ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ሽፈራው ተሊላ እንዳሉት÷ የተቀላጠፈና አስተማማኝ የኤሌክትሪክ አገልግሎት ለህብረተሰቡ ተደራሽ ለማድረግ በትኩረት እየሰራ ነው፡፡በተጠናቀቀው 2016 በጀት ዓመት 427 ሺህ በላይ አዳዲስ ደንበኞችን ማፍራት መቻሉን ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ተናግረዋል፡፡በ2016 በጀት ዓመት በከተለያዩ የገቢ ምንጮች 42 ቢሊየን ብር ገቢ ማግኘት መቻሉንም ዋና ሥራ አስፈጻሚው ገልጸዋል፡፡የኤሌክትሪክ መቆራረጥ ችግርን ለመቅረፍም ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በትብብር እየተሰራ መሆኑን አንስተዋል፡፡የኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ መስመሮችን አቅም የማሳደግ፣ የመፈተሽና የመጠገን ሥራዎች እየተከናወኑ እንደሚገኙም አመልክተዋል፡፡
Woreda to World
More Stories
ባለፉት ሦስት ዓመታት ለሰብዓዊ ድጋፍ በሚል የገባ ስንዴ የለም – አምባሳደር ሽፈራው ተክለማርያም (ዶ/ር)
በገጠሩ የሀገሪቱ አካባቢዎች መንግስት የሚዘረጋቸውን የተለያዩ ኢንሸቲቦችን ቀድሞና ፈጥኖ ተግባራዊ ከማድረግ አንፃር የተሻሉ አፈጻጸሞች መታየታቸው ተገለፀ ።
የሚኒስትሮች ምክር ቤት በ6 ጉዳዮች ላይ ውሳኔ አሳለፈ