የአገልግሎቱ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ሽፈራው ተሊላ እንዳሉት÷ የተቀላጠፈና አስተማማኝ የኤሌክትሪክ አገልግሎት ለህብረተሰቡ ተደራሽ ለማድረግ በትኩረት እየሰራ ነው፡፡በተጠናቀቀው 2016 በጀት ዓመት 427 ሺህ በላይ አዳዲስ ደንበኞችን ማፍራት መቻሉን ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ተናግረዋል፡፡በ2016 በጀት ዓመት በከተለያዩ የገቢ ምንጮች 42 ቢሊየን ብር ገቢ ማግኘት መቻሉንም ዋና ሥራ አስፈጻሚው ገልጸዋል፡፡የኤሌክትሪክ መቆራረጥ ችግርን ለመቅረፍም ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በትብብር እየተሰራ መሆኑን አንስተዋል፡፡የኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ መስመሮችን አቅም የማሳደግ፣ የመፈተሽና የመጠገን ሥራዎች እየተከናወኑ እንደሚገኙም አመልክተዋል፡፡
Woreda to World
More Stories
ዜጎች በመልዕክት መላላኪያ አማራጮች በሚፈጸሙ የሳይበር ጥቃቶች ተጋላጭ እንዳይሆኑ ጥንቃቄ ማድረግ ይኖርባቸዋል፡-የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር
በሸካ ዞን አስተማማኝና ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥ እና የህግ የበላይነትን ለማስከበር ያለመ ዞናዊ የፀጥታ ግብረ ኃይል የምክክር መድረክ በቴፒ ከተማ ተካሄደ
ክልላዊ የተቀናጀ የማኅበረሰብ አቀፍ ተፋሰስ ልማት ማብሰሪያ ፕሮግራም በመካሄድ ላይ ይገኛል።