አረብ ኤምሬትስ ሁለቱ ሀገራት ምርኮኞችን እንዲለዋወጡ የማደራደሩን ሚና ተወጥታለች
ኤምሬትስ ሩሲያና ዩክሬን የእስረኞች ልውውጥ ስምምነት እንዲደርሱ ስታደርግ የዛሬው ለሰባተኛ ጊዜ ነው ተብሏልሩሲያ እና ዩክሬን በዛሬው እለት የጦር ምርኮኞችን ተለዋውጠዋል።በአረብ ኤምሬትስ አደራዳሪነት ከስምምነት በተደረሰው የእስረኞች ልውውጥ ሁለቱ ሀገራት እኩል 115 እስረኞችን ተለዋውጠዋል ብሏል አናዶሉ በዘገባው።ዩክሬን ከ18 ቀናት በፊት በምዕራባዊ ሩሲያ ኩርስክ ክልል ጥቃት ከከፈተች በኋላ ከሞስኮ ጋር ለመጀመሪያ ጊዜ ነው የእስረኞች ልውውጥ ያደረገችው።ሩሲያ የለቀቀቻቸው የዩክሬን ወታደሮች የሀገራቸውን ብሄራዊ መዝሙር ሲዘምሩ ታይተዋል።
Al-Ain
More Stories
እየተጠናከረ የመጣው የብሪክስ ሀገራት ግንኙነት…
አሜሪካ ሶሪያን አጠቃች
የሩሲያ ጦር በፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን መኖሪያ ቤት ላይ ተፈጽሟል ላለው ጥቃት አፀፋ በዩክሬን ላይ መጠነ ሰፊ ጥቃት መፈጸሙን አስታውቋል።