ክብሩን፣ ድሉን፣ ውጤቱን፣ ምስጋናውን ፈጣሪ ይውሰድና፤ ማልደን የተነሳንበት ኢትዮጵያን በ600 ሚሊዮን ችግኞች አረንጓዴ የማልበስ ሕልም 615.7 ሚሊዮን ችግኞችን በመትከል የታለመለትን ፍሬ በማፍራቱ እጅግ ደስ ብሎኛል ብለዋል አቶ አደም ፋራህ።ህፃናት፣ አረጋውያን፣ ሴቶች እና ወጣቶች ስለ ነገዋ ኢትዮጵያችን ብለው፣ ትውልድን አስበው አፈር እየማሱ ደፋ ቀና ሲሉ ማየት ልብን በሃሴት ይሞላል ነው ያሉት በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ሃላፊ እና የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንት አደም ፋራህ።በዘር፣ በፆታ፣ በእድሜ፣ በሙያ ሳንከፋፈል ስለ ኢትዮጵያ እና ስለ ትውልዷ ብለን ዛሬ ላይ የሰራነው ገድል ነገ በታሪክ ዘንድ ወርቃማ ካባ እንደሚያጎናፅፈን ፈፅሞ ጥርጥር የለውም ብለዋል አቶ አደም ፋራህ በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባጋሩት የደስታ መግለጫ መልዕክት።ዛሬ የተከልነውንም ተንከባክበን በማፅደቅ፣ የአረንጓዴ አሻራ ትጋታችንን በእጥፍ በመጨመር የኢትዮጵያ ብልፅግና እና ስልጣኔ በዛፎች እና በተፈጥሯዊ በረከቶች መሀል እንዲዋቀር የበኩላችንን ኃላፊነት መወጣታችንን እንቀጥላለን፤ እንኳን ደስ አለን፣ እንኳን ደስ አላችሁ ብለዋል።
ኢትዮጵያን አረንጓዴ የማልበስ ሕልማችን የታለመለትን ፍሬ በማፍራቱ እጅግ ደስ ብሎኛል – አቶ አደም ፋራህ
More Stories
እንግሊዝን ያስቆጣው የኢራን ጥቃት
በሸካ ዞን ቴፒ ከተማ በሌማት ትሩፋት መርሐግብር የተሠማሩ ወጣቶች ተጠቃሚ እየሆኑ መምጣቸው ተገለጸ።
ኢራን ላይ እየተካሄደ የሚገኘው ወታደራዊ ዘመቻ …