በኢትዮጵያ የሩሲያ አምባሳደር ኢቭጌኒ ተረክሂን የተመራ ልዑካን ቡድን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደርን የስራ እንቅስቃሴ ጎብኝቷል፡፡ የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር ትዕግስት ሃሚድ ሀገራዊ የሳይበር ደህንነትን ለማረጋገጥ በተቋሙ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን አስመልክቶ ለቡድኑ ገለጻ አድርገዋል። በሳይበር ደህንነት ዘርፍ በሁለቱ ሀገራት መካከል የተጀመረውን ሁሉን አቀፍ የትብብር ስራ ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር እንደሚሰራም ገልጸዋል። በኢትዮጵያ የሩሲያ አምባሳደር ኢቭጌኒ ተረክሂን የጉብኝቱ ዓላማ የኢትዮጵያን የሳይበር ደህንነት ልምድ መመልከትና ሁለቱ ሀገራት በዘርፉ ያላቸውን ትብብር ማጠናከር መሆኑን አመልክተዋል። ኢትዮጵያ በሳይበር ደህንነት ዘርፍ፤ በተለይም ደግሞ የቴክኖሎጂና የዕውቀት ባለቤትነትን በማረጋገጥ ረገድ ከፍተኛ ስራ መስራቷን ከጉብኝቱ መረዳታቸውን ጠቁመዋል፡፡ ኢትዮጵያ የሳይበር ደህንነቷን እና ሉዓላዊነቷን ለማረጋገጥ በምታደርገው ጥረት ሩሲያ ያላትን ልምድ ከማካፈል ጀምሮ በጋራ ለመስራት ከፍተኛ ፍላጎት እንዳላት አምባሳደሩ መናገራቸውን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት
EBC
More Stories
መንግስት በፈጠራና ክህሎት ላይ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ነው – ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ
ሀገራዊ የጤና ፖሊሲ ከመከላከልባሻገር አክሞ መዳንን መሰረት ያደረገ ስራን መስራት እንደሚገባ ተገለፀ።
በኢራን ወደብ በደረሰ ፍንዳታ 25 ሰዎች ህይወታቸው አለፈ