የአሽንዳ በዓል ባህላዊ እና ኃይማኖታዊ እሴቱን ጠብቆ ለቀጣዩ ትውልድ እንዲተላለፍ እየተሰራ መሆኑን፤ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ባህልና ቱሪዝም ቢሮ አስታውቋል፡፡ ቢሮው በዓሉን አስመልክቶ የሴቶች ሁለንተናዊ ተጠቃሚነትን ማሳደግ ላይ ያተኮረ የፓናል ውይይት አካሄዷል፡፡ በፓናል ውይይቱ ላይ አሸንዳን የቱሪስት መስህብ ማድረግ በሚቻልበት አግባብ ላይ ምክክር ተደርጓል፡፡ በተመሳሳይ በመቐለ ከተማ ሮማናት አደባባይ የአሸንዳ የካርኒቫል ሥነ-ሥርዓት መካሄዱ ታውቋል፡፡ በነገው ዕለትም የጊዜያዊ አስተዳደሩ ከፍተኛ አመራሮች እና ከተለያዩ አካባቢዎች የመጡ እንግዶች በተገኙበት የአሸንዳ በዓል በድምቀት እንደሚከበር ተመላክቷል፡፡
የአሽንዳ በዓል እሴቱን ጠብቆ ለቀጣዩ ትውልድ እንዲተላለፍ እየተሰራ ነው – የትግራይ ክልል ባህልና ቱሪዝም ቢሮ
More Stories
ዜጎች በመልዕክት መላላኪያ አማራጮች በሚፈጸሙ የሳይበር ጥቃቶች ተጋላጭ እንዳይሆኑ ጥንቃቄ ማድረግ ይኖርባቸዋል፡-የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር
በሸካ ዞን አስተማማኝና ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥ እና የህግ የበላይነትን ለማስከበር ያለመ ዞናዊ የፀጥታ ግብረ ኃይል የምክክር መድረክ በቴፒ ከተማ ተካሄደ
ክልላዊ የተቀናጀ የማኅበረሰብ አቀፍ ተፋሰስ ልማት ማብሰሪያ ፕሮግራም በመካሄድ ላይ ይገኛል።