ሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ በጎፋ ዞን ገዜ ጎፋ ወረዳ በመሬት መንሸራተት አደጋ ለተጎዱ ወገኖች የ25 ሚሊየን ብር ድጋፍ አድርጓል፡፡ ድጋፉን ሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕን በመወከል አቶ ያዕቁብ ፈቂ፤ ለጎፋ ዞን ዋና አሰተዳደሪ ዳግማዊ አየለ (ኢ/ር) አስረክበዋል፡፡ ከድጋፉ ውስጥ 10 ሚሊየን ብር ለተጎጂዎች አፋጣኝ እርዳታ፣ 15 ሚሊየን ብር ደግሞ አካባቢውን በዘላቂነት ለማልማት የሚውል መሆኑ ተጠቁሟል፡፡ ዋና አስተዳዳሪው ለተደረገው ድጋፍ ምስጋና አቅርበው፤ ተጎጂዎችን በዘላቂነት መልሶ ለማቋቋም እየተደረገ ያለው ድጋፉ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡ የሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ በዞኑ በደረሰው የመሬት መንሸራተት አደጋ የተሰማውን ሐዘን በድጋሚ ገልጾ ለተጎጂዎች መጽናናትን ተመኝቷል፡፡
EBC
More Stories
የአየር ጠባይ ትንበያ መረጃ የታላቁ ሕዳሴ ግድብ የውኃ ሙሌት በታቀደው መሠረት እንዲከናወን ድርሻውን ተውጥቷል – ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፋ(ዶ/ር)
መጪው የበጋ የአየር ጠባይ ወቅቱን ያልጠበቀ ዝናብ በሚኖርባቸው አካባቢዎች በደረሱ ሰብሎች ላይ ተጽዕኖ ሊያደርስ ይችላል ተባለ።
የወባ መከላከያ ክትባት በሽታውን ለማጥፋት በማለም ለተጀመረው ርብርብ ትልቅ እገዛ ያደርጋል አሉ የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ደረጄ ዱጉማ።