ሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ በጎፋ ዞን ገዜ ጎፋ ወረዳ በመሬት መንሸራተት አደጋ ለተጎዱ ወገኖች የ25 ሚሊየን ብር ድጋፍ አድርጓል፡፡ ድጋፉን ሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕን በመወከል አቶ ያዕቁብ ፈቂ፤ ለጎፋ ዞን ዋና አሰተዳደሪ ዳግማዊ አየለ (ኢ/ር) አስረክበዋል፡፡ ከድጋፉ ውስጥ 10 ሚሊየን ብር ለተጎጂዎች አፋጣኝ እርዳታ፣ 15 ሚሊየን ብር ደግሞ አካባቢውን በዘላቂነት ለማልማት የሚውል መሆኑ ተጠቁሟል፡፡ ዋና አስተዳዳሪው ለተደረገው ድጋፍ ምስጋና አቅርበው፤ ተጎጂዎችን በዘላቂነት መልሶ ለማቋቋም እየተደረገ ያለው ድጋፉ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡ የሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ በዞኑ በደረሰው የመሬት መንሸራተት አደጋ የተሰማውን ሐዘን በድጋሚ ገልጾ ለተጎጂዎች መጽናናትን ተመኝቷል፡፡
EBC
More Stories
የሕዳሴ ግድብን የግንባታ ሥራ ለመጀመር ከኮንትራቱ ውጪ 1 ቢሊየን ዩሮ ከፍለናል – ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የአረፋ(ዒድ አል አድሃ) በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት
መጋቢት 24 ቀን 2010 ዓ.ም የተገቡ ቃሎች አንድ በአንድ እየተተገበሩ ናቸው – ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር)