የሀገር መከላከያ ሠራዊት የሀገርን ሉዓላዊነት እና ሰላም ከማረጋገጥ ባለፈ በልማቱ ላይ እያደረገ ያለው ተሳትፎ አበረታች ነው ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር ) ገለጹ፡፡ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር ) በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት ጽሁፍ እንደገለጹት ÷መከላከያ ሠራዊት የሰላም ምንጭ ብቻ ሳይሆን የልማት እና የፈጠራ ምንጭ መሆን ስላለበት በዚህ አግባብ እየተመራ እየተገኘ ያለው ውጤት ተስፋ ሰጭ ነው ፡፡ይህም ተስፋ ሰጭ ተግባር ተጠናክሮ መቀጠል ይኖርበታል ነው ያሉት ።በስንዴ ምርት በእርሻ በ #አረንጓዴዓሻራ ብዙ የኢንዱስትሪ ውጤቶችን በማምረት ልማቱን ለማሳለጥ እና የብልፅግና መሰረት ለመጣል እያደረገ ያለው ጥረት ሊበረታታ እንደሚገባም ገልጸዋል፡፡
FBC
More Stories
ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከዳያስፖራው ማህበረሰብ አጀንዳ ማሰባሰብ ጀመረ
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክር ቤት የዘርፍ ቋሚ ኮሚቴዎች የ2017 በጀት አመት የአስፈፃሚ አካላት አፈፃፀም ግምገማ መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።
ማህበረሰቡ በከባድ ዝናብ ምክንያት ከሚከሰቱ አደጋዎች እንዲጠነቀቅ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አሳሰበ።