የጋምቤላ ህዝቦች ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው አስቸኳይ ጉባዔ ወይዘሮ አለሚቱ ኡሞድን በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አድርጎ ሾሟል። የክልሉ ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው 6ኛ ዙር 3ኛ የስራ ዘመን 2ኛ አስቸኳይ ጉባኤ ነው ለርዕሰ መስተዳድሯ ሹመቱን የሰጠው፡፡ አዲስ ሹመት የተከናወነው ወቅቱ የሚጠይቀውን አሻጋሪ የለውጥ አመራር በማምጣት የህዝቡ የሰላም፣ የልማትና የመልካም አስተዳደር ፍላጎቶች በተገቢው መንገድ ምላሽ እንዲያገኙ ለማስቻል እንዲሁም የቀድሞው የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኡሞድ ኡጁሉ በገዥው ፓርቲ ለሌላ ተልዕኮ በመፈለጋቸው መሆኑም ተጠቅሷል። ወይዘሮ ዓለሚቱ አሞድ ቀደም ሲል የክልሉ ምክትል አፈ- ጉባኤ፣ የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ በመሆንና በሌሎች የተለያዩ ከፍተኛ የስራ ኃላፊነቶች ሲያገለግሉ መቆየታቸው ተጠቁሟል፡፡ ወይዘሮ አለሚቱ ኡሞድ በክልሉ ታሪክ የመጀመሪያዋ ሴት ርዕሰ መስተዳድር መሆናቸውም ተገልጿል። በሚፍታህ አብዱልቃድር
EBC
More Stories
ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከዳያስፖራው ማህበረሰብ አጀንዳ ማሰባሰብ ጀመረ
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክር ቤት የዘርፍ ቋሚ ኮሚቴዎች የ2017 በጀት አመት የአስፈፃሚ አካላት አፈፃፀም ግምገማ መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።
ማህበረሰቡ በከባድ ዝናብ ምክንያት ከሚከሰቱ አደጋዎች እንዲጠነቀቅ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አሳሰበ።