አባስ በዛሬው እለት በቱርክ ፓርላማ በመገኘት በፍልስጤም ወቅታዊ ሁኔታ ገለጻ ያደርጋሉየፍልስጤም አስተዳደር ፕሬዝዳንት ማህሙድ አባስ በአንካራ ከቱርኩ ፕሬዝዳንት ሬሲፕ ጣይብ ኤርዶሃን ጋር ተወያዩ።በዝግ የተካሄደው ምክክር “እስራኤል በፍልስጤማውያን ላይ እየፈጸመችው ባለው ጭፍጨፋ እና ዘላቂ የተኩስ አቁም ስምምነት ለመድረስ በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ ነበር” ብሏል የፕሬዝዳንት ኤርዶሃን ጽህፈት ቤት።እስራኤል በሃማስን የጥቅምት 7 ጥቃት ተከትሎ በጋዛ የምትፈጽመውን ጥቃት አጥብቀው የሚቃወሙት ኤርዶሃን፥ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁንን ከአዶልፍ ሂትለር ጋር እስከማመሳሰል መድረሳቸው ይታወሳል።አሜሪካ እና የአውሮፓ ህብረት በሽብርተኛ ድርጅትነት የመዘገቡትን ሃማስም “የነጻነት ታጋይ” ነው በማለት ማወደሳቸውም አይዘነጋም።
Al-Ain
More Stories
የአውሮፓ ህብረት ያወጣቸውን ደንቦች መሠረት በማድረግ የግብርና ምርቶች ከደን ጭፍጨፋ ነፃ ሆነው እንዲመረቱ ከማድረግ አንፃር የግብርና ባለሙያዎች ሚና የጎላ እንደሆነ ተገለፀ ።
ትራምፕ ቲክ ቶክን የሚገዙ የአሜሪካ ባለሀብቶች ማግኘታቸውን ገለፁ
ሩሲያ እና ህንድ በጦር መሳሪያ አቅርቦት ላይ ያላቸውን ትብብር ለማሳደግ እንደሚሰሩ አስታወቁ፡፡