ኢትዮጵያና ሶማሊያ ሁለተኛውን ዙር ውይይት ማድረጋቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ አስታውቀዋል፡፡የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ባሰፈሩት መልዕክት÷በቱርክ አመቻችነት በኢትዮጵያና በሶማሊያ መካከል 2ኛ ዙር ዉይይት በአንካራ መካሄዱን ገልጸዋል።አምባሳደር ታዬ የቱርክ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሃከን ፊዳን ከውይይቱ በፊት ኢትዮጵያን በመጎብኘታቸው ምስጋና አቅርበዋል።“የኢትዮጵያ የባህር በር ለማግኘት ያላት ህጋዊ ፍላጎትም በሰላማዊ መንገድ ከጎረቤቶቻችን ጋር በመተባበር እንደሚፈፀም እርግጠኛ ነኝ” ሲሉም ገልጸዋል።
FBC
More Stories
ዜጎች በመልዕክት መላላኪያ አማራጮች በሚፈጸሙ የሳይበር ጥቃቶች ተጋላጭ እንዳይሆኑ ጥንቃቄ ማድረግ ይኖርባቸዋል፡-የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር
በሸካ ዞን አስተማማኝና ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥ እና የህግ የበላይነትን ለማስከበር ያለመ ዞናዊ የፀጥታ ግብረ ኃይል የምክክር መድረክ በቴፒ ከተማ ተካሄደ
ክልላዊ የተቀናጀ የማኅበረሰብ አቀፍ ተፋሰስ ልማት ማብሰሪያ ፕሮግራም በመካሄድ ላይ ይገኛል።