ኢትዮጵያና ሶማሊያ ሁለተኛውን ዙር ውይይት ማድረጋቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ አስታውቀዋል፡፡የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ባሰፈሩት መልዕክት÷በቱርክ አመቻችነት በኢትዮጵያና በሶማሊያ መካከል 2ኛ ዙር ዉይይት በአንካራ መካሄዱን ገልጸዋል።አምባሳደር ታዬ የቱርክ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሃከን ፊዳን ከውይይቱ በፊት ኢትዮጵያን በመጎብኘታቸው ምስጋና አቅርበዋል።“የኢትዮጵያ የባህር በር ለማግኘት ያላት ህጋዊ ፍላጎትም በሰላማዊ መንገድ ከጎረቤቶቻችን ጋር በመተባበር እንደሚፈፀም እርግጠኛ ነኝ” ሲሉም ገልጸዋል።
FBC
More Stories
ባለፉት ሦስት ዓመታት ለሰብዓዊ ድጋፍ በሚል የገባ ስንዴ የለም – አምባሳደር ሽፈራው ተክለማርያም (ዶ/ር)
በገጠሩ የሀገሪቱ አካባቢዎች መንግስት የሚዘረጋቸውን የተለያዩ ኢንሸቲቦችን ቀድሞና ፈጥኖ ተግባራዊ ከማድረግ አንፃር የተሻሉ አፈጻጸሞች መታየታቸው ተገለፀ ።
የሚኒስትሮች ምክር ቤት በ6 ጉዳዮች ላይ ውሳኔ አሳለፈ