የብልጽግና ፓርቲ ወጣቶች ሊግ ሥራ አስፈጻሚ አባላት በጋምቤላ ክልል የችግኝ ተከላ መርሐ ግብር አከናውነዋል፡፡
የብልጽግና ፓርቲ ወጣቶች ሊግ ፕሬዚዳንት አክሊሉ ታደሰ በዚህ ወቅት እንዳሉት÷የአባላቱን ተጠቃሚነት ማረጋገጥ የሚያስችሉ በርካታ ተግባራት እየተከናወኑ ነው ።
ሊጉ አባላቱን በማስተባበር ባለፈው ዓመት በመላ ሀገሪቱ ከ460 ሚሊየን በላይ ችግኝ መትከሉን አስታውሰዋል።
የብልፅግና ፓርቲ ወጣቶች ሊግ ከ3 ነጥብ 5 ሚሊየን በላይ አባላት እንዳለው ጠቁመው÷በዘንድሮው ዓመት 500 ሚሊየን ችግኝ ለመትከል ታቅዶ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።
የሊጉ አባላት በበኩላቸው÷የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት አንድነትን በማጠናከር ሁለተናዊ ብልጽግናን ለማረጋገጥ ያግዛል ብለዋል።
በተያዘው ክረምት በመላ ሀገሪቱ አባላትን በማስተባበር ችግኞችን በመትከል የአረጓዴ አሻራ መርሐ ግብርን የመደገፍ ሥራ እየተከናወነ መሆኑን አብራርተዋል።
የተራቆቱ አከባቢዎች በደን ለመሸፈን እየተደረገ ባለው ጥረት ችግኞችን በየጊዜው መንከባከብ እንደሚያስፈልግ መጠቆማቸውንም የክልሉ ኮሙኒኬሽን መረጃ ያመላክታል፡፡
FBC
More Stories
ዜጎች በመልዕክት መላላኪያ አማራጮች በሚፈጸሙ የሳይበር ጥቃቶች ተጋላጭ እንዳይሆኑ ጥንቃቄ ማድረግ ይኖርባቸዋል፡-የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር
በሸካ ዞን አስተማማኝና ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥ እና የህግ የበላይነትን ለማስከበር ያለመ ዞናዊ የፀጥታ ግብረ ኃይል የምክክር መድረክ በቴፒ ከተማ ተካሄደ
ክልላዊ የተቀናጀ የማኅበረሰብ አቀፍ ተፋሰስ ልማት ማብሰሪያ ፕሮግራም በመካሄድ ላይ ይገኛል።