በደጋማው አካባቢ በጣለው ከፍተኛ ዝናብ ምክንያት በጎግ፣ በላሬ፣ በጆር እና በዋንቱዋ ወረዳዎች በሚገኙ ቀበሌዎች ላይ የጎርፍ መጥለቅለቅ መከሰቱን የጋምቤላ ክልል አደጋ ስጋት ስራ አመራር አስታወቀ፡፡
በተከሰተው የጎርፍ አደጋም ከ16 ሺህ በላይ ነዋሪዎች ከቀያቸው መፈናቀላቸውን እና ለጊዜው ደረቃማ በሆኑ አካባቢዎች እንዲሰፍሩ መደረጉ ተጠቅሷል፡፡
ከክልሉ መንግሥትና ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት በመነጋገር ለተፈናቃዮቹ አፋጣኝ ድጋፍ የሚደርስበት ሁኔታ እንደሚመቻችም ተጠቁሟል፡፡
የጎርፍ አደጋው በቤት ውስጥ ያሉ ቁሳቁሶችን ጨምሮ በቁም እንስሳትና ሰብል ላይ ጉዳት ማድረሱን የክልሉ ኮሙኒኬሽን ቢሮ መረጃ አመላክቷል፡፡
FBC
More Stories
የሕዳሴ ግድብን የግንባታ ሥራ ለመጀመር ከኮንትራቱ ውጪ 1 ቢሊየን ዩሮ ከፍለናል – ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የአረፋ(ዒድ አል አድሃ) በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት
መጋቢት 24 ቀን 2010 ዓ.ም የተገቡ ቃሎች አንድ በአንድ እየተተገበሩ ናቸው – ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር)