በደጋማው አካባቢ በጣለው ከፍተኛ ዝናብ ምክንያት በጎግ፣ በላሬ፣ በጆር እና በዋንቱዋ ወረዳዎች በሚገኙ ቀበሌዎች ላይ የጎርፍ መጥለቅለቅ መከሰቱን የጋምቤላ ክልል አደጋ ስጋት ስራ አመራር አስታወቀ፡፡
በተከሰተው የጎርፍ አደጋም ከ16 ሺህ በላይ ነዋሪዎች ከቀያቸው መፈናቀላቸውን እና ለጊዜው ደረቃማ በሆኑ አካባቢዎች እንዲሰፍሩ መደረጉ ተጠቅሷል፡፡
ከክልሉ መንግሥትና ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት በመነጋገር ለተፈናቃዮቹ አፋጣኝ ድጋፍ የሚደርስበት ሁኔታ እንደሚመቻችም ተጠቁሟል፡፡
የጎርፍ አደጋው በቤት ውስጥ ያሉ ቁሳቁሶችን ጨምሮ በቁም እንስሳትና ሰብል ላይ ጉዳት ማድረሱን የክልሉ ኮሙኒኬሽን ቢሮ መረጃ አመላክቷል፡፡
FBC
More Stories
ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከዳያስፖራው ማህበረሰብ አጀንዳ ማሰባሰብ ጀመረ
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክር ቤት የዘርፍ ቋሚ ኮሚቴዎች የ2017 በጀት አመት የአስፈፃሚ አካላት አፈፃፀም ግምገማ መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።
ማህበረሰቡ በከባድ ዝናብ ምክንያት ከሚከሰቱ አደጋዎች እንዲጠነቀቅ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አሳሰበ።