በፓሪስ 2024 የኦሊምፒክ ወድድር በማራቶን ኢትዮጵያ በአትሌት ታምራት ቶላ አማካኝነት የመጀመሪያ ወርቋን አግኝታለች፡፡
በፓሪስ ኦሊምፒክ የወንዶች የማራቶች ውድድር የተካሄደ ሲሆን ÷አትሌት ቀነኒሳ በቀለ፣ ታምራት ቶላና ደሬሳ ገሌታ ኢትዮጵያን ወክለው ተወዳድረዋል።
በዚህም ታምራት ቶላ ውድድሩን 2 ሰዓት ከ6 ደቂቃ ከ26 ሰከንድ በመግባት በቀዳሚነት በማጠናቀቅ በኦሊምፒኩ ለኢትዮጵያ የመጀመሪያውን የወርቅ ሜዳሊያ አስገኝቷል፡፡
አትሌት ደሬሳ ገለታ ደግሞ ውድድሩን በአምስተኛ ደረጃ አጠናቋል፡፡
More Stories
የ2026 የካራባኦ ዋንጫ ፍፃሜ …
ሴኔጋል የአፍሪካ ዋንጫ ሻምፒዮንነቷ እንዲሰረዝ መወሰኑ አሳፋሪ ነው፡- የካፍ ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ኦጉስቲን ሴንግሆር
ቦርንማውዝ ከ ማንችስተር ዩናይትድ