የገቢዎች ሚኒስቴር ከመካከለኛ ግብር ከፋዮች ጋር በታክስ ህግ ተገዥነት እና በወቅታዊ አገራዊ ጉዳይ ዙሪያ ውይይት እያካሄደ ነው። በመድረኩ ንግግር ያደረጉት የገንዘብ ሚኒስትሩ አህመድ ሺዴ፤ የመንግስት ዋነኛ ትኩረት ከግብር የሚገኘውን ገቢ ማሳደግ መሆኑን ተናግረዋል። የገቢ አሰባሰቡ ህግና ስርዓትን የተከተለ እንዲሆን ለማስቻል በመንግስት የሚመራ ግብረ ሀይል ተቋቁሞ እየተሰራ ነው ብለዋል። የሀገር ውስጥ ገቢን ለማሳደግ ተቋማት በጋራ እንዲሰሩም ጥሪ አቅርበዋል። የገቢዎች ሚኒስትሯ አይናለም ንጉሴ በበኩላቸው፤ የገቢ አሰባሰቡን ለማሳደግ በቀጣይ ዓመታት 5 ዋና ዋና ስትራቴጂክ እቅዶች ተነድፈው እንቅስቃሴ ተጀምሯል ብለዋል።
በተያዘው በጀት ዓመት የመንግስት ዋነኛ ትኩረት ገቢን ማሳደግ ነው ሲሉ የገንዘብ ሚኒስትሩ አህመድ ሺዴ ተናገሩ።

More Stories
ባለፉት ሦስት ዓመታት ለሰብዓዊ ድጋፍ በሚል የገባ ስንዴ የለም – አምባሳደር ሽፈራው ተክለማርያም (ዶ/ር)
በገጠሩ የሀገሪቱ አካባቢዎች መንግስት የሚዘረጋቸውን የተለያዩ ኢንሸቲቦችን ቀድሞና ፈጥኖ ተግባራዊ ከማድረግ አንፃር የተሻሉ አፈጻጸሞች መታየታቸው ተገለፀ ።
የሚኒስትሮች ምክር ቤት በ6 ጉዳዮች ላይ ውሳኔ አሳለፈ