የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ በጎፋ ዞን በገዜ ጎፋ ወረዳ ተፈጥሮ በነበረው የመሬት መንሸራተት በደረሰው አደጋ የተጎዱ ወገኖችን በዘላቂነት ለማቋቋም የተጀመሩ ስራዎችን በመገምገም ቀጣይ አቅጣጫዎችን አስቀምጠዋል፡፡ ችግሩ ከተከሰተበት ጊዜ ጀምሮ የክልሉ መንግስት ከተለያዩ ተቋማት የተውጣጡ ኮሚቴዎችን በማቋቋም የአስቸኳይ ጊዜ ስራዎች ብሎም በዘላቂነት የሚፈጸሙ ስራዎችን ሲያከናውን መቆየቱ ተገልጿል። በዚህም በአደጋው ለተጎዱ ወገኖች የሚደረገው ድጋፍ ተጠናክሮ የቀጠለ ሲሆን÷ የተሰበሰበውን ሀብት በአግባቡ በመያዝ ደረጃውን የጠበቀ ስርጭት እና የአስተዳደር ስርአት መከተል እንደሚገባ አቶ ጥላሁን ተናግረዋል። በአደጋው የተጎዱ ሰዎች ቤተሰቦችን በዘላቂነት ለማስፈር እና መልሶ ለማቋቋም እየተከናወነ የሚገኘው የመኖሪያና የእርሻ ቦታ መረጣና ዝግጅት በጥናት የተደገፈ መሆን እንዳለበት አስገንዝበዋል። ሂደቱም የህዝቡን ተሳትፎ ያረጋገጠ እንዲሆን ርዕሰ መስተዳድሩ ማሳሰባቸውን ከክልሉ መንግስት ኮሙኒኬሽን ቢሮ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡
EBC
More Stories
የአየር ጠባይ ትንበያ መረጃ የታላቁ ሕዳሴ ግድብ የውኃ ሙሌት በታቀደው መሠረት እንዲከናወን ድርሻውን ተውጥቷል – ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፋ(ዶ/ር)
መጪው የበጋ የአየር ጠባይ ወቅቱን ያልጠበቀ ዝናብ በሚኖርባቸው አካባቢዎች በደረሱ ሰብሎች ላይ ተጽዕኖ ሊያደርስ ይችላል ተባለ።
የወባ መከላከያ ክትባት በሽታውን ለማጥፋት በማለም ለተጀመረው ርብርብ ትልቅ እገዛ ያደርጋል አሉ የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ደረጄ ዱጉማ።