በሶማሌ ክልል በምግብ ሸቀጦች ላይ ያልተገባ የዋጋ ጭማሪ ባደረጉ 57 የንግድ ድርጅቶች ላይ እርምጃ ተወስዷል፡፡
የማክሮ ኢኮኖሚ ፖሊሲ ማሻሻያውን ተከትሎ በጅግጅጋ፣ ቀብሪደሀር እና ጎዴ ከተሞች በምግብ ሸቀጦች ላይ ያልተገባ የዋጋ ጭማሪ ባደረጉ ነጋዴዎች ላይ እርምጃ መወሰዱን የክልሉ ንግድና ትራንስፖርት ቢሮ አስታውቋል፡፡
ማሻሻያውን ተከትሎ አንዳንድ ነጋዴዎች በዘይት፣ ሩዝ፣ ፓስታ፣ ስኳር፣ ዱቄት እና ማካሮኒ ላይ ያልተገባ የዋጋ ጭማሪ ማድረጋቸውን በተደረገ ክትትል ማረጋገጡን የቢሮው ምክትል ኃላፊ አብዱላሂ አደን ለኢቲቪ ተናግረዋል።
በዚህም ያልተገባ የዋጋ ጭማሪ ያደረጉ 57 የንግድ ድርጅቶች ሲታሸጉ፤ ከ1 ሺህ 2 መቶ ለሚበልጡ ነጋዴዎችም ግንዛቤ መፍጠር መቻሉን ምክትል ኃላፊው ገልጸዋል፡፡
ያለ በቂ ምክንያት የንግድ ቦታቸውን በመዝጋት እና በመጋዘን በማከማቸት የምግብ ሸቀጦች ዋጋ እንዲንር አስተዋፅኦ አድርገዋል በተባሉ ድርጅቶች ላይም ከፅሑፍ ማስጠንቀቂያ እስከ አስተዳደራዊ እርምጃ መወሰዱን አመላክተዋል፡፡
በህገ ወጥ ነጋዴዎች ላይ እየተወሰደ የሚገኘው እርምጃ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የጠቆመው ቢሮው ነጋዴዎች ከመሰል ድርጊት እንዲቆጠቡም አሳስቧል።
FBC
More Stories
እንግሊዝን ያስቆጣው የኢራን ጥቃት
በሸካ ዞን ቴፒ ከተማ በሌማት ትሩፋት መርሐግብር የተሠማሩ ወጣቶች ተጠቃሚ እየሆኑ መምጣቸው ተገለጸ።
ኢራን ላይ እየተካሄደ የሚገኘው ወታደራዊ ዘመቻ …