የማክሮ ኢኮኖሚ ለውጡን በቁንጽል ሳይሆን በምልዐት መመልከት ይገባል ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አስገነዘቡ፡፡ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው እንዳሉት፥ የማክሮ ኢኮኖሚ ለውጡን በቁንጽል ሳይሆን በምልዐት መመልከት ይገባል። በመደመር ዕሳቤያችን ለሀገር ልማት ምን መደረግ እንዳለበት በጥልቀት መዝነን አስቀምጠናል ያሉ ሲሆን፥ ዓላማችን የኢትዮጵያን ብልጽግና ማረጋገጥ ነው ብለዋል፡፡አካሄዳችን ድሃ ተኮር፤ ትኩረታችን ለችግር በመጠቃት ተጋላጭ የሆኑ ደካሞችን መደገፍ ነው ሲሉም ነው የገለጹት። የለውጥ ሥራዎቻችን ሁሉ ስኬት በባለድርሻ አካላት የተባበረ ጥረት ላይ ይመሠረታል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፥ ይህም ምርታማነትን፣ የውጭ ንግድንና ገቢን ተባብሮ ማሳደግ ማለት እንደሆነ አንስተዋል፡፡የሕግ አስፈጻሚ አካላት የለውጥ ሥራውን ባልተገባ ሕገ-ወጥ መንገድ ለመጠቀም በሚፈልጉ ስግብግብ ነጋዴዎች ላይ እርምጃ እንዲወስዱ ኃላፊነት እንደተሰጣቸውም ነው የገለጹት። እነዚህን ሃሳቦችም ዛሬ ጠዋት ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር በነበራቸው መድረክ መግለጻቸውን ጠቅሰው፥ የበለጠ ዝርዝር መረጃ ለማግኘት የመድረኩን ውይይት በሚዲያዎች መከታተል እንደሚቻል አመላክተዋል።
FBC
More Stories
ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከዳያስፖራው ማህበረሰብ አጀንዳ ማሰባሰብ ጀመረ
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክር ቤት የዘርፍ ቋሚ ኮሚቴዎች የ2017 በጀት አመት የአስፈፃሚ አካላት አፈፃፀም ግምገማ መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።
ማህበረሰቡ በከባድ ዝናብ ምክንያት ከሚከሰቱ አደጋዎች እንዲጠነቀቅ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አሳሰበ።