ሙሉ በሙሉ በነዳጅ የሚሰሩ በታሪፍ መፅሐፉ አንቀፅ 87.03 የሚመደቡ ሙሉ በሙሉ ተገጣጥመው የቀረቡ የቤት አውቶሞቢሎች እና ባለሶስት እግር ተሽከርካሪዎች ላይ የተጣለው ዕገዳ እንደተጠበቀ ሆኖ በተቀሩት ዕቃዎች ላይ የተጣለው የውጭ ምንዛሪ ገደብ ውሳኔ ከነማሻሻያው የተሻረ መሆኑን የገንዘብ ሚኒስቴር አስታወቀ።መንግሥት በቁጥር ክሂገ 1/7/252 በቀን 04/02/2015 በተላለፈ ውሳኔ እና በቁጥር ታፖመ/ፖ/29/16 በቀን 28/6/2016 በተሻሻለው መሰረት በተወሰኑ ዕቃዎች ላይ የባንክ የውጭ ምንዛሪ ገደብ እንዲጣል ማድረጉ ይታወሳል።አሁን ላይ ሙሉ በሙሉ በነዳጅ የሚሰሩ በታሪፍ መፅሐፉ አንቀፅ 87.03 የሚመደቡ ሙሉ በሙሉ ተገጣጥመው የቀረቡ የቤት አውቶሞቢሎች እና ባለሶስት እግር ተሽከርካሪዎች ላይ የተጣለው እገዳ እንደተጠበቀ ሆኖ በተቀሩት ዕቃዎች ላይ የተጣለው የውጭ ምንዛሪ ገደብ ውሳኔ ከነማሻሻያው ከሐምሌ 21 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ የተሻረ መሆኑን የገንዘብ ሚኒስቴር አስታውቋል።
EBC
More Stories
የ2017 ዓ.ም የዩኒቨርሲቲ መውጫ ፈተና መሰጠት ጀመረ
ሀገራዊ ለውጡን ተከትሎ ለክልሎች የሚከፋፈለው የጋራ ገቢ የድጎማ በጀት እያደገ መጥቷል፦ የፌዴሬሽን ምክር ቤት
ከኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ የተሰጠ ወቅታዊ መረጃ