በመቐለ፣ አዲግራት፣ አክሱም እና ራያ ዩኒቨርሲቲዎች ሁለተኛው ዙር የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና እየተሰጠ ይገኛል። በመቐለ ዩኒቨርሲቲ ዋና ግቢ ተገኝተው ፈተናውን ያስጀመሩት የትግራይ ክልል ጊዚያዊ አስተዳደር ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጌታቸው ረዳ ተማሪዎች በፈተናው የላቀ ውጤት ለማስመዝገብ እንዲሰሩ መልእክት አስተላልፈዋል። ተፈታኝ ተማሪዎች የተሻለ ውጤት በማስመዝገብ ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት እንዲገቡ መልካም ምኞታቸውንም ገልፀዋል። በትግራይ ክልል ጊዚያዊ አስተዳደር የክልሉ ትምህርት ቢሮ ሀላፊ ዶክተር ኪሮስ ጉዕሽ በሁለተኛው ዙር የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተና በአራቱም ዩኒቨርሲቲዎች 23ሺህ ተማሪዎች ለፈተና መቀመጣቸውን አስታውቀዋል። ተፈታኞች በ2013/14 ትምህርት ዘመን በቀድሞ ስርአተ ትምህርት ተምረው በተለያዩ ምክንያቶች ፈተናውን ሳይወስዱ የቆዩ መሆናቸው መመላከቱን ኢዜአ ዘግቧል።
EBC
More Stories
ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከዳያስፖራው ማህበረሰብ አጀንዳ ማሰባሰብ ጀመረ
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክር ቤት የዘርፍ ቋሚ ኮሚቴዎች የ2017 በጀት አመት የአስፈፃሚ አካላት አፈፃፀም ግምገማ መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።
ማህበረሰቡ በከባድ ዝናብ ምክንያት ከሚከሰቱ አደጋዎች እንዲጠነቀቅ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አሳሰበ።