በጀርመን አስተናጋጅነት ሲካሄድ የቆየው 17ኛው የአውሮፓ ዋንጫ በስፔን አሸናፊነት ተጠናቅቋል፡፡ በበርሊን ኦሊምፒክ ስታዲየም በተካሄደው የፍጻሜ ጨዋታ ስፔን እንግሊዝን 2 ለ 1 በማሸነፍ ለአራተኛ ጊዜ የዋንጫው ባለቤት ሆናለች፡፡ በጨዋታው የስፔንን የማሸነፊያ ግቦች ኒኮ ዊሊያም እና ማይክል ኦያርዛባል በ47ኛው እና በ86ኛው ደቂቃ አስቆጥረዋል፡፡ እንግሊዝን ከሽንፈት ያልታደገችውን ብቸኛ ግብ ተቀይሮ የገባው ኮል ፓልመር በ73ኛው ደቂቃ አስቆጥሯል፡፡ በውድድሩ አስደናቂ ብቃት ሲያሳይ የቆየው የ17 ዓመቱ ኮከብ ላሚን ያማል በዚህም ጨዋታ ለግብ የሚሆን ኳስ አመቻችቶ በማቀበል ውድድሩን በስኬት አጠናቋል፡፡
EBC
More Stories
የሸካ ዞን የታዳጊ ወጣቶች የእግርኳስ ቡድን የ2018 ክልል አቀፍ ውድድር የዋንጫ አሸናፊ ሆነ።
5ተኛው የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የባህል ስፖርቶች ውድድር፣ የባህል ፌስቲቫል እና የታዳጊ ወጣቶች ምዘና ውድድር የታለመውን ግብ ያሳካ መሆኑ ተገለጸ።
ባካሪ ሳኛ ኢትዮጵያ ገባ