በ2016 በጀት ዓመት በአስቸኳይ የሙስና መከላከል ሥራ ከ2 ነጥብ 8 ቢሊየን ብር በላይ ከሙስና እና ከምዝበራ ማዳን መቻሉን የፌደራል የስነ-ምግባር እና ፀረ ሙስና ኮሚሽን አስታወቀ ።
በኮሚሽኑ የአስቸኳይ ሙስና መከላከል መሪ ሥራ አስፈፃሚ አቶ ገዛኸኝ ጋሻው÷ በ2016 በጀት ዓመት በተከናወኑ አበይት ጉዳዮች ዙሪያ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል።
በመግለጫቸውም÷ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ175 ሺህ በላይ አመራርና ሰራተኞች ሃብታቸውን ማስመዝገባቸውን አንስተዋል፡፡
በክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች 1 ሺህ 87 አስቸኳይ የሙስና መከላከል ሥራ መከናወኑን ነው የተናገሩት፡፡
በዚህም 2 ነጥብ 8 ቢሊየን ብር እና 8 ሺህ 490 የአሜሪካ ዶላር ማዳን መቻሉን ጠቁመው÷ ከመሬት ጋር በተያያዘም ከ46 ሚሊየን ካሬ ሜትር የከተማና የገጠር ቦታ ከሙስና ምዝበራ ማዳን ተችሏል ብለዋል፡፡
አስቸኳይ የሙስና መከላከል ሥራው ከግዥ፣ መሬት አሰጣጥ፣ ንብረት ማስወገድ፣ ገቢ አሰባሰብ ፣ ዕርዳታ አሰጣጥ እና ከማዳበሪያ ስርጭት ጋር የተያያዘ እንደሆነ መጥቀሳቸውን ኢዜአ ዘግቧል፡፡
FBC
More Stories
ባለፉት ሦስት ዓመታት ለሰብዓዊ ድጋፍ በሚል የገባ ስንዴ የለም – አምባሳደር ሽፈራው ተክለማርያም (ዶ/ር)
በገጠሩ የሀገሪቱ አካባቢዎች መንግስት የሚዘረጋቸውን የተለያዩ ኢንሸቲቦችን ቀድሞና ፈጥኖ ተግባራዊ ከማድረግ አንፃር የተሻሉ አፈጻጸሞች መታየታቸው ተገለፀ ።
የሚኒስትሮች ምክር ቤት በ6 ጉዳዮች ላይ ውሳኔ አሳለፈ