በ2016 በጀት ዓመት በአስቸኳይ የሙስና መከላከል ሥራ ከ2 ነጥብ 8 ቢሊየን ብር በላይ ከሙስና እና ከምዝበራ ማዳን መቻሉን የፌደራል የስነ-ምግባር እና ፀረ ሙስና ኮሚሽን አስታወቀ ።
በኮሚሽኑ የአስቸኳይ ሙስና መከላከል መሪ ሥራ አስፈፃሚ አቶ ገዛኸኝ ጋሻው÷ በ2016 በጀት ዓመት በተከናወኑ አበይት ጉዳዮች ዙሪያ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል።
በመግለጫቸውም÷ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ175 ሺህ በላይ አመራርና ሰራተኞች ሃብታቸውን ማስመዝገባቸውን አንስተዋል፡፡
በክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች 1 ሺህ 87 አስቸኳይ የሙስና መከላከል ሥራ መከናወኑን ነው የተናገሩት፡፡
በዚህም 2 ነጥብ 8 ቢሊየን ብር እና 8 ሺህ 490 የአሜሪካ ዶላር ማዳን መቻሉን ጠቁመው÷ ከመሬት ጋር በተያያዘም ከ46 ሚሊየን ካሬ ሜትር የከተማና የገጠር ቦታ ከሙስና ምዝበራ ማዳን ተችሏል ብለዋል፡፡
አስቸኳይ የሙስና መከላከል ሥራው ከግዥ፣ መሬት አሰጣጥ፣ ንብረት ማስወገድ፣ ገቢ አሰባሰብ ፣ ዕርዳታ አሰጣጥ እና ከማዳበሪያ ስርጭት ጋር የተያያዘ እንደሆነ መጥቀሳቸውን ኢዜአ ዘግቧል፡፡
FBC
More Stories
እንግሊዝን ያስቆጣው የኢራን ጥቃት
በሸካ ዞን ቴፒ ከተማ በሌማት ትሩፋት መርሐግብር የተሠማሩ ወጣቶች ተጠቃሚ እየሆኑ መምጣቸው ተገለጸ።
ኢራን ላይ እየተካሄደ የሚገኘው ወታደራዊ ዘመቻ …